Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 131 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የመ​ዓ​ርግ መዝ​ሙር።

1 አቤቱ፥ ዳዊ​ትን፥ ገር​ነ​ቱ​ንም ሁሉ ዐስብ፤

2 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ማለ፥ ለያ​ዕ​ቆ​ብም አም​ላክ እንደ ተሳለ፦

3 “ወደ ቤቴ ድን​ኳን አል​ገ​ባም፥ ወደ መኝ​ታ​ዬም አልጋ አል​ወ​ጣም፥

4 ለዐ​ይ​ኖቼም መኝ​ታን፥ ለቅ​ን​ድ​ቦ​ቼም እን​ቅ​ል​ፍን፥ ለጕ​ን​ጮ​ቼም ዕረ​ፍ​ትን አል​ሰ​ጥም፥

5 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቦታ፥ የያ​ዕ​ቆብ አም​ላ​ክን ማደ​ሪያ እስ​ካ​ገኝ ድረስ” ብሎ እንደ ተሳለ ዐስብ።

6 እነሆ፥ በኤ​ፍ​ራታ ሰማ​ነው፥ ዛፍ በበ​ዛ​በ​ትም ቦታ አገ​ኘ​ነው።

7 እን​ግ​ዲ​ህስ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማደ​ሪ​ያ​ዎች እን​ገ​ባ​ለን፤ የጌ​ታ​ችን እግ​ሮቹ በሚ​ቆ​ሙ​በት ቦታ እን​ሰ​ግ​ዳ​ለን።

8 አቤቱ፥ ወደ ዕረ​ፍ​ትህ ተነሥ፥ አን​ተና የመ​ቅ​ደ​ስህ ታቦት።

9 ካህ​ና​ትህ ጽድ​ቅን ይለ​ብ​ሳሉ፥ ጻድ​ቃ​ን​ህም ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

10 ስለ ባሪ​ያህ ስለ ዳዊት ቀብ​ተህ ካነ​ገ​ሥ​ኸው ፊት​ህን አት​መ​ልስ።

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለዳ​ዊት እን​ዲህ ሲል በእ​ው​ነት ማለ፥ አይ​ጸ​ጸ​ት​ምም፥ “ከሆ​ድህ ፍሬ በዙ​ፋ​ንህ ላይ አስ​ቀ​ም​ጣ​ለ​ሁና

12 ልጆ​ችህ ኪዳ​ኔን፥ ይህ​ንም የማ​ስ​ተ​ም​ራ​ቸ​ውን ምስ​ክ​ሬን ቢጠ​ብቁ፥ ልጆ​ቻ​ቸው በዙ​ፋ​ንህ ላይ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይቀ​መ​ጣሉ።”

13 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጽዮ​ንን መር​ጦ​አ​ታ​ልና፥ ማደ​ሪ​ያ​ውም ትሆ​ነው ዘንድ ወድ​ዶ​አ​ታ​ልና፥

14 “ይህች ለዘ​ለ​ዓ​ለም ማረ​ፊ​ያዬ ናት፤ መር​ጫ​ታ​ለ​ሁና በዚ​ህች አድ​ራ​ለሁ።

15 ባል​ቴ​ቶ​ች​ዋን እጅግ እባ​ር​ካ​ቸ​ዋ​ለሁ፥ ድሆ​ች​ዋ​ንም እህ​ልን አጠ​ግ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ፥

16 ካህ​ና​ቷ​ንም ደኅ​ን​ነ​ትን አለ​ብ​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ፥ ጻድ​ቃ​ኖ​ች​ዋም እጅግ ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

17 በዚያ ለዳ​ዊት ቀን​ድን አበ​ቅ​ላ​ለሁ፥ ቀብቼ ላነ​ገ​ሥ​ሁ​ትም መብ​ራ​ትን አዘ​ጋ​ጃ​ለሁ።

18 ጠላ​ቶ​ቹ​ንም እፍ​ረ​ትን አለ​ብ​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በእ​ር​ሱም ቅድ​ስ​ናዬ ያፈ​ራል።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos