Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 ሰነፍ በልቡ፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የለም” ይላል። በሥ​ራ​ቸው ረከሱ፥ ጐሰ​ቈ​ሉም፤ በጎ ነገ​ርን የሚ​ሠ​ራት የለም። አን​ድም እንኳ የለም።

2 የሚ​ያ​ስ​ተ​ውል፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም የሚ​ፈ​ልግ እን​ዳለ ያይ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከሰ​ማይ የሰው ልጆ​ችን ተመ​ለ​ከተ።

3 ሁሉ ተስ​ተ​ካ​ክሎ በአ​ን​ድ​ነት ዐመፀ፤ በጎ ነገ​ርን የሚ​ሠ​ራት የለም፤ አን​ድም እንኳ የለም።

4 ጕሮ​ሮ​ኣ​ቸው እንደ መቃ​ብር የተ​ከ​ፈተ ነው፥ በም​ላ​ሳ​ቸው ሸነ​ገሉ፤

5 ከከ​ን​ፈ​ራ​ቸው በታች የእ​ባብ መርዝ አለ፤ አፋ​ቸው መራራ ነው፥ መር​ገ​ም​ንም ተሞ​ል​ቶ​አል፤

6 ደምን ለማ​ፍ​ሰስ እግ​ራ​ቸው ፈጣን ነው፤ ጥፋ​ትና ጕስ​ቍ​ልና በመ​ን​ገ​ዳ​ቸው አለ፥ የሰ​ላ​ምን መን​ገድ አላ​ወ​ቁ​አ​ት​ምና፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት በዐ​ይ​ና​ቸው ፊት የለም።

7 ሕዝ​ቤን እንደ እን​ጀራ የሚ​በሉ፥ ኀጢ​አ​ትን የሚ​ሠሩ ሁሉ አያ​ው​ቁም። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አይ​ጠ​ሩ​ትም።

8 በዚ​ያም ፈሩ፥ የማ​ያ​ስ​ፈ​ራ​ውም አስ​ፈ​ራ​ቸው። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጻ​ድ​ቃን ትው​ልድ ዘንድ ነውና።

9 የድ​ሆ​ችን ምክር አሳ​ፈ​ራ​ችሁ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ተስ​ፋ​ቸው ነው።

10 ከጽ​ዮን መድ​ኀ​ኒ​ትን ለእ​ስ​ራ​ኤል ማን ይሰ​ጣል? እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሕ​ዝ​ቡን ምርኮ በመ​ለሰ ጊዜ፥ ያዕ​ቆብ ደስ ይለ​ዋል፥ እስ​ራ​ኤ​ልም ሐሤ​ትን ያደ​ር​ጋል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos