መዝሙር 124 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)የመዓርግ መዝሙር። 1 በእግዚአብሔር የታመኑ እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው፥ በኢየሩሳሌም የሚኖር ለዘለዓለም አይታወክም። 2 ተራሮች ይከቧታል፥ ከዛሬ ጀምሮ ለዘለዓለም እግዚአብሔር ሕዝቡን ይመግባል። 3 ጻድቃን እጃቸውን በዐመፃ እንዳይዘረጉ እግዚአብሔር የኃጥኣንን በትር በጻድቃን ዕጣ ላይ አይተውምና። 4 አቤቱ፥ ለቸሮች፥ ልባቸውም ለቀና መልካምን አድርግ። 5 ወደ ጠማማነት የሚመለሱትን ግን ዐመፃን ከሚሠሩት ጋር እግዚአብሔር ይወስዳቸዋል። ሰላም በእስራኤል ላይ ይሁን። |