Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 117 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሃሌ ሉያ።

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግኑ፥ ቸር ነውና፥ ምሕ​ረቱ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና።

2 ቸር እንደ ሆነ፥ ምሕ​ረቱ ለዘ​ለ​ዓ​ለም እንደ ሆነ፥ የእ​ስ​ራ​ኤል ወገን ንገሩ።

3 ቸር እንደ ሆነ፥ ምሕ​ረቱ ለዘ​ለ​ዓ​ለም እንደ ሆነ፥ የአ​ሮን ወገን ንገሩ።

4 ቸር እንደ ሆነ፥ ምሕ​ረቱ ለዘ​ለ​ዓ​ለም እንደ ሆነ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈሩ ሁሉ ንገሩ።

5 በተ​ጨ​ነ​ቅሁ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ጠራ​ሁት፤ ሰማኝ፥ አሰ​ፋ​ል​ኝም።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ረዳቴ ነው፥ አል​ፈ​ራም፤ ሰው ምን ያደ​ር​ገ​ኛል?

7 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ረዳቴ ነው፥ እነሆ፥ በጠ​ላ​ቶቼ ላይ አያ​ለሁ።

8 በሰው ከመ​ታ​መን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መታ​መን ይሻ​ላል።

9 በአ​ለ​ቆች ተስፋ ከማ​ድ​ረግ ይልቅ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተስፋ ማድ​ረግ ይሻ​ላል።

10 አሕ​ዛብ ሁሉ ከበ​ቡኝ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስም አሸ​ነ​ፍ​ኋ​ቸው፤

11 መክ​በ​ቡ​ንስ ከበ​ቡኝ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስም አሸ​ነ​ፍ​ኋ​ቸው፤

12 ንብ ማርን እን​ደ​ሚ​ከ​ብብ ከበ​ቡኝ፥ እሳ​ትም በእ​ሾህ ውስጥ እን​ደ​ሚ​ነ​ድድ ነደዱ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስም አሸ​ነ​ፍ​ኋ​ቸው።

13 ለመ​ው​ደ​ቅም ተን​ገ​ደ​ገ​ድሁ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን አነ​ሣኝ።

14 ኀይ​ሌም ስም አጠ​ራ​ሬም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፥ እር​ሱም አዳኜ ሆነኝ።

15 የደ​ስታ ድምፅ በጻ​ድ​ቃን ማደ​ሪ​ያ​ዎች ነው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀኝ ኀይ​ልን አደ​ረ​ገች።

16 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀኝ ከፍ ከፍ አደ​ረ​ገ​ችኝ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀኝ ኀይ​ልን አደ​ረ​ገች።

17 አል​ሞ​ትም በሕ​ይ​ወት እኖ​ራ​ለሁ እንጂ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሥራ እና​ገ​ራ​ለሁ።

18 መገ​ሠ​ጽስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ገሠ​ጸኝ፤ ለሞት ግን አሳ​ልፎ አል​ሰ​ጠ​ኝም።

19 የጽ​ድ​ቅን ደጆች ክፈ​ቱ​ልኝ፤ ወደ እነ​ርሱ ገብቼ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ግን ዘንድ።

20 ይህች የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ደጅ ናት፤ ወደ እር​ስዋ ጻድ​ቃን ይገ​ባሉ።

21 ሰም​ተ​ኸ​ኛ​ልና፥ አዳ​ኜም ሆነ​ኸ​ኛ​ልና አቤቱ፥ አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ።

22 ግን​በ​ኞች የና​ቋት ድን​ጋይ፥ እርሷ የማ​ዕ​ዘን ራስ ሆነች፥

23 ይህች ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ሆነች፥ ለዐ​ይ​ኖ​ቻ​ች​ንም ድንቅ ናት።

24 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሠ​ራት ቀን ይህች ናት፤ በእ​ር​ስዋ ደስ ይበ​ለን፥ ሐሤ​ት​ንም እና​ድ​ር​ግ​ባት።

25 አቤቱ፥ እባ​ክህ፥ አሁን አድን፤ አቤቱ፥ እባ​ክህ፥ አሁን አቅና።

26 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም የሚ​መጣ ቡሩክ ነው፤ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት መረ​ቅ​ና​ችሁ።

27 ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተገ​ለ​ጠ​ልን፤ እስከ መሠ​ዊ​ያው ቀን​ዶች ድረስ በሚ​ያ​ስ​ተ​ነ​ት​ኑ​በት በደ​ስታ በዓ​ልን አድ​ርጉ።

28 አንተ አም​ላኬ ነህ፥ አመ​ሰ​ግ​ን​ህ​ማ​ለሁ። አንተ አም​ላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍም አደ​ር​ግ​ሃ​ለሁ፤ ሰም​ተ​ኸ​ኛ​ልና፥ አዳ​ኜም ሆነ​ኸ​ኛ​ልና አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ።

29 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግኑ፥ ቸር ነውና፥ ምሕ​ረቱ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos