Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 109 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 ጌታ ጌታ​ዬን፥ “ጠላ​ቶ​ች​ህን ለእ​ግ​ርህ መረ​ገጫ እስ​ካ​ደ​ር​ግ​ልህ ድረስ በቀኜ ተቀ​መጥ” አለው።

2 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የኀ​ይ​ልን በትር ከጽ​ዮን ይል​ክ​ል​ሃል፤ በጠ​ላ​ቶ​ች​ህም መካ​ከል ትገ​ዛ​ለህ።

3 ቀዳ​ማዊ፦ በኀ​ይል ቀን፥ በቅ​ዱ​ሳን ብር​ሃን ከአ​ንተ ጋር ነበር፥ ከአ​ጥ​ቢያ ኮከብ አስ​ቀ​ድሞ ከሆድ ወለ​ድ​ሁህ።

4 እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት አንተ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ካህን ነህ ብሎ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማለ አይ​ጸ​ጸ​ት​ምም።

5 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቀ​ኝህ ነው፥ ነገ​ሥ​ታ​ትን በቍ​ጣው ቀን ይቀ​ጠ​ቅ​ጣ​ቸ​ዋል።

6 በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ይፈ​ር​ዳል፥ ሬሳ​ዎ​ች​ንም ያበ​ዛል፤ በም​ድር ላይ የብ​ዙ​ዎ​ችን ራሶች ይቀ​ጠ​ቅ​ጣል።

7 በመ​ን​ገድ ከፈ​ሳሽ ውኃ ጠጡ፤ ስለ​ዚህ ራስ ከፍ ከፍ ይላል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos