Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ዮዲት 9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የዮ​ዲት ጸሎት

1 ዮዲት ግን በግ​ን​ባሯ ተደ​ፍታ በም​ድር ላይ ወደ​ቀች፤ በራ​ሷም ላይ ትቢያ ነሰ​ነ​ሰች፤ የም​ት​ለ​ብ​ሰ​ው​ንም ማቅ አሳ​የች፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ የሠ​ርክ ዕጣን በሚ​ቀ​ር​ብ​በት ጊዜ ዮዲት በታ​ላቅ ቃል ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኸች፤ እን​ዲ​ህም አለች፦

2 “በማ​ኅ​ፀን ያለ ጽን​ስን ያጠፉ፥ ድን​ግ​ል​ንም ያጐ​ሰ​ቈሉ፥ ልብ​ሷ​ንም የገ​ፈፉ፥ በከ​ተ​ማም በአ​ራቱ ማዕ​ዘን ለመ​ገ​ዳ​ደር ማኅ​ፀ​ንን ያሳ​ደፉ ጠላ​ቶ​ችን ይበ​ቀል ዘንድ በእጁ ሰይ​ፍን የሰ​ጠ​ኸው የአ​ባቴ የስ​ም​ዖን አም​ላክ ሆይ፥ አንተ እን​ዲህ አይ​ደ​ለም አልህ፤ እነ​ርሱ ግን አደ​ረ​ጉት።

3 ስለ​ዚ​ህም አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ውን ለመ​ገ​ደል አሳ​ል​ፈህ ሰጠ​ሃ​ቸው፤ መኝ​ታ​ቸ​ውም በተ​ገ​ደ​ሉት ባሮች ደም ተነ​ከረ፤ ባሮ​ችን ከጌ​ቶ​ቻ​ቸው ጋር፥ ጌቶ​ች​ንም በዙ​ፋ​ኖ​ቻ​ቸው ላይ ገደ​ል​ሃ​ቸው።

4 ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ልጆ​ቻ​ቸው ተማ​ረኩ፤ በአ​ንተ ዘንድ የተ​ወ​ደዱ፥ ለአ​ም​ላ​ክ​ነ​ት​ህም የቀኑ፥ የረ​ከሰ ደማ​ቸ​ው​ንም የተ​ጸ​የፉ፥ ትረ​ዳ​ቸ​ውም ዘንድ የለ​መኑ የል​ጆ​ችን ምርኮ ሁሉ ተካ​ፈሉ፤ አም​ላኬ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆይ፥ እኔን መበ​ለ​ቲ​ቱን ስማኝ።

5 ከዚህ አስ​ቀ​ድ​ሞና ከዚ​ያም በኋላ የሆ​ነ​ውን አንተ አድ​ር​ገ​ሃ​ልና የዛ​ሬ​ው​ንና የሚ​መ​ጣ​ው​ንም ታው​ቀ​ዋ​ለህ፤ አን​ተም በም​ታ​ው​ቀው ሆነ።

6 ምክ​ርህ የቀና ነው፤ ሥር​ዐ​ትህ የተ​ዘ​ጋጀ ነውና፥ ፍር​ድ​ህ​ንም አስ​ቀ​ድ​መህ ባወ​ቅህ ፈር​ደ​ሃ​ልና እነሆ፥ መጣን ይሉ​ሃል፤

7 “እነሆ፥ የአ​ሦር ሰዎች ከሠ​ራ​ዊ​ታ​ቸው ጋር በዝ​ተ​ዋ​ልና፥ በፈ​ረ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ላይ ከፍ ከፍ ብለ​ዋ​ልና፥ በፈ​ረ​ስም የተ​ቀ​መጡ ሰዎች በኀ​ይ​ላ​ቸው ታም​ነ​ዋ​ልና፥ አር​በ​ኞ​ችም በጽ​ና​ታ​ቸው፥ በቀ​ስ​ታ​ቸ​ውና በጦ​ራ​ቸው፥ በም​ድር ነጎ​ዳ​ቸ​ውም ታም​ነ​ዋ​ልና አንተ አር​በ​ኞ​ችን የም​ታ​ጠፋ አም​ላክ እንደ ሆንህ አላ​ወ​ቁ​ህ​ምና ስም​ህም አሸ​ናፊ እንደ ሆነ አል​ተ​ገ​ነ​ዘ​ቡም።

8 አንተ ከሠ​ራ​ዊ​ታ​ቸው ጋር በከ​ሃ​ሊ​ነ​ትህ አጥ​ፋ​ቸው፤ ቤተ መቅ​ደ​ስን ያጐ​ሰ​ቍሉ ዘንድ፥ የስ​ምህ ጌት​ነት ማደ​ሪያ የሆ​ነች ደብ​ተራ ኦሪ​ት​ንም ያሳ​ድፉ ዘንድ መክ​ረ​ዋ​ልና፥ በብ​ረ​ትም የመ​ሠ​ዊ​ያ​ህን ቀን​ዶች አፍ​ር​ሰ​ዋ​ልና በቍ​ጣህ ኀይ​ላ​ቸ​ውን አጥፋ።

9 ትዕ​ቢ​ታ​ቸ​ውን ተመ​ል​ከት፤ በራ​ሳ​ቸ​ውም ላይ ቍጣ​ህን አምጣ። እንደ አሰ​ብ​ሁት እፈ​ጽም ዘንድ በእኔ በመ​በ​ለ​ቲቱ እጅ ኀይ​ልን አድ​ርግ።

10 በአ​ን​ደ​በቴ ጥበብ ሎሌ​ውን ከጌ​ታው፥ ጌታ​ው​ንም ከሎ​ሌው ጋር ግደል። ግር​ማ​ቸ​ውን በእኔ በሴ​ቲቱ እጅ አጥፋ።

11 ብር​ታ​ትህ በብ​ዙ​ዎች አይ​ደ​ለ​ምና፥ ኀይ​ል​ህም በኀ​ያ​ላን ሰዎች አይ​ደ​ለ​ምና፤ ነገር ግን አንተ የት​ሑ​ታን አም​ላክ ነህ፤ የጥ​ቂ​ቶች ረዳት ነህ፤ የበ​ሽ​ተ​ኞ​ችም ፈዋሽ አንተ ነህ፤ ለጠ​ፉ​ትም ጠባ​ቂ​ያ​ቸው አንተ ነህ፤ ተስፋ የቈ​ረጡ ሰዎ​ች​ንም የም​ታ​ድ​ና​ቸው አንተ ነህ።

12 አወን አቤቱ የአ​ባቴ አም​ላክ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም የር​ስ​ታ​ቸው አም​ላክ፥ የሰ​ማ​ይና የም​ድር አም​ላክ፥ ውኃ​ውን የፈ​ጠ​ርህ፥ የፍ​ጥ​ረ​ታት ሁሉ ንጉሥ አንተ ጸሎ​ቴን ስማ።

13 የቃ​ሌ​ንም ጥበብ በሕ​ግ​ህና በቤተ መቅ​ደ​ስህ በደ​ብረ ጽዮ​ንና በል​ጆ​ችህ ንብ​ረት ቤት ላይ ክፉ ነገ​ርን የመ​ከሩ ጠላ​ቶ​ችን እን​ዲ​ያ​ቈ​ስ​ላ​ቸ​ውና እን​ዲ​ያ​ጠ​ፋ​ቸው አድ​ርግ።

14 የብ​ር​ታ​ትና የኀ​ይል ሁሉ አም​ላክ አንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንህ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ወገን ከአ​ንተ በቀር ሌላ የሚ​ያ​ጸ​ና​ቸው እንደ ሌለ ለሕ​ዝ​ቡና ለአ​ሕ​ዛቡ ሁሉ እን​ዲ​ያ​ው​ቁት አድ​ርግ።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos