Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ዮዲት 2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


በም​ዕ​ራብ በኩል በሚ​ገኙ ሕዝ​ቦች የተ​ደ​ረገ ጦር​ነት

1 በዐ​ሥራ ስም​ን​ተ​ኛው ዓመት በጨ​ረቃ አቈ​ጣ​ጠር በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር በሰ​ባ​ተ​ኛው ቀን እንደ ተና​ገ​ረው ሀገ​ሩን ሁሉ ይበ​ቀል ዘንድ በአ​ሦር ንጉሥ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ቤተ መን​ግ​ሥት ምክር ተመ​ከረ።

2 ሹሞ​ቹ​ንና አለ​ቆ​ቹን ሁሉ ጠርቶ ከእ​ነ​ርሱ ጋር የም​ክ​ሩን ምሥ​ጢር ተነ​ጋ​ገረ፤ በሀ​ገሩ ሁሉ ክፉ ነገ​ርን ተና​ገረ።

3 በአ​ን​ደ​በቱ የተ​ና​ገ​ረ​ውን ትእ​ዛዝ ያል​ተ​ቀ​በ​ሉ​ትን ሰዎች ሁሉ ያጠ​ፋ​ቸው ዘንድ ምክር ጨረሱ።

4 ከዚ​ህም በኋላ ምክ​ሩን በጨ​ረሱ ጊዜ የአ​ሦር ንጉሥ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ከእ​ርሱ በታች ያለ ቢት​ወ​ደዱ ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ጠርቶ እን​ዲህ አለው፦

5 “የአ​ገሩ ሁሉ ጌታ ገና​ናው ንጉሥ እን​ዲህ ይላል፦ መቶ ሃያ ሺህ በኀ​ይ​ላ​ቸው የታ​መኑ እግ​ረ​ኞች ሰዎ​ችን መቶ ሃያ ሺህ ፈረ​ሰ​ኞ​ች​ንም ከፈ​ረ​ሶ​ቻ​ቸው ጋራ ካንተ ጋራ ይዘህ እነሆ በፊቴ ትወ​ጣ​ለህ።

6 በአ​ን​ደ​በቴ ለተ​ና​ገ​ር​ሁት ነገር መታ​ዘ​ዝን እንቢ ብለ​ዋ​ልና በም​ዕ​ራብ በኩል ወዳ​ለች ሀገር ትወ​ጣ​ለህ።

7 በእ​ነ​ርሱ ተቈ​ጥቼ እወ​ጣ​ለ​ሁና፥ ምድ​ር​ንም በሠ​ራ​ዊቴ እግር እሸ​ፍ​ና​ታ​ለ​ሁና፥ ገን​ዘ​ባ​ቸ​ው​ንም እዘ​ር​ፋ​ቸ​ዋ​ለሁ፥ እበ​ረ​ብ​ራ​ቸ​ዋ​ለ​ሁ​ምና ውኃ​ው​ንና ሀገ​ሩን ያዘ​ጋ​ጁ​ልኝ ዘንድ ለእ​ነ​ርሱ አዋጅ ትነ​ግ​ራ​ለህ።

8 ቍስ​ለ​ኞ​ቻ​ቸ​ውም በሸ​ለ​ቆ​ውና በፈ​ሳሹ ይመ​ላሉ፤ ወን​ዙም ሬሳ​ቸ​ውን ተመ​ልቶ ይፈ​ስ​ሳል፤

9 ምር​ኳ​ቸ​ው​ንም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ እበ​ት​ነ​ዋ​ለሁ።

10 አንተ ግን ቀድ​መህ አው​ራ​ጃ​ዎ​ቻ​ቸ​ውን ሁሉ ያዝ​ልኝ፤ ራሳ​ቸ​ውን ወዳ​ንተ ቢመ​ልሱ በእ​ነ​ርሱ እስ​ከ​ም​ፈ​ር​ድ​በት ቀን ለእኔ ትጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋ​ለህ።

11 ዐመ​ፀ​ኞ​ችን ታጠ​ፋ​ቸው ዘንድ፤ በሄ​ድ​ህ​በ​ትም ሁሉ ትዘ​ር​ፋ​ቸው ዘንድ ዐይ​ንህ አት​ራ​ራ​ላ​ቸው።

12 እኔ ሕያው ነኝና እንደ ተና​ገ​ር​ሁም ይኽን በእጄ አደ​ርግ ዘንድ መን​ግ​ሥቴ ጽኑዕ ነውና።

13 እን​ዳ​ዘ​ዝ​ሁህ አድ​ርግ እንጂ አን​ተም ከእኔ ከጌ​ታህ ቃል አን​ዲት ስንኳ የም​ት​ተ​ወው አይ​ኑር፤ ይህ​ንም ፈጥ​ነህ አድ​ርግ።”


የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ዘመቻ

14 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም ከጌ​ታው ፊት ወጥቶ ኀያ​ላ​ኑን፥ አዛ​ዦ​ች​ንና የአ​ሦር ሠራ​ዊት አለ​ቆ​ችን ሁሉ ጠራ​ቸው።

15 ጌታ​ውም እን​ዳ​ዘ​ዘው መቶ ሃያ ሺህ የተ​መ​ረጡ እግ​ረ​ኞች አር​በ​ኞ​ች​ንና ዐሥራ ሁለት ሺህ ፈረ​ሰ​ኞች ቀስ​ተ​ኞ​ችን ቈጠረ።

16 ፈጽ​መው ይዋጉ ዘንድ አዘ​ዛ​ቸው።

17 ስን​ቃ​ቸ​ው​ንም የሚ​ጭ​ኑ​ባ​ቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ግመ​ሎ​ች​ንና አህ​ዮ​ችን፥ በቅ​ሎ​ዎ​ች​ንም፥ ምግ​ብም ሊሆ​ኗ​ቸው ቍጥር የሌ​ላ​ቸው በሬ​ዎ​ች​ንና በጎ​ችን፥ ፍየ​ሎ​ች​ንም ወሰደ።

18 ለብዙ ሰዎ​ችና ለሠ​ራ​ዊቱ ሁሉ ከን​ጉሡ ቤት እጅግ ብዙ የሆነ ብርና ወር​ቅን ስንቅ አድ​ርጎ ሰጣ​ቸው።

19 እር​ሱም ከሠ​ራ​ዊቱ ሁሉ ጋር ወጣ፤ በፈ​ረ​ሶ​ችና በሠ​ረ​ገ​ላ​ዎች፥ በተ​መ​ረጡ አር​በ​ኞ​ችም በም​ዕ​ራብ አን​ጻር ያለ ምድ​ርን ሁሉ ይሸ​ፍን ዘንድ ከን​ጉሡ አስ​ቀ​ድሞ ዘመተ።

20 ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር አንድ የሆኑ፥ ብዛ​ታ​ቸ​ውም እንደ አን​በ​ጣና እንደ ባሕር አሸዋ የሆኑ ብዙ ሰዎች ከእ​ነ​ርሱ ጋር ወጡ። ከብ​ዛ​ታ​ቸ​ውም የተ​ነሣ ቍጥር የላ​ቸ​ውም።

21 ከነ​ነ​ዌም ወጥ​ተው በበ​ቄ​ጤ​ሊት ሜዳ አን​ጻር የሦ​ስት ቀን ጎዳና ሄዱ፤ ከላ​ይ​ኛው ቂል​ቅያ በስ​ተ​ግራ በኩል ባለው ተራራ አጠ​ገብ በበ​ቄ​ጤ​ሊት አን​ጻር ሰፈሩ።

22 ከዚ​ያም ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ሠራ​ዊ​ቱን ሁሉ፥ ፈረ​ሰ​ኞ​ች​ንና እግ​ረ​ኞ​ች​ንም፥ ሠረ​ገ​ላ​ዎ​ች​ንም ይዞ ወደ ተራ​ራ​ማው ሀገር ሄደ።

23 ፌድ​ንና ሎድ​ንም ወጋ​ቸው፤ የሬ​ስ​ስን ልጆ​ችን ሁሉ፥ በኤ​ሌ​ዎን ግራ አን​ጻር ባለ ሜዳ የሚ​ኖሩ የእ​ስ​ማ​ኤ​ል​ንም ልጆች ማረ​ካ​ቸው።

24 ኤፍ​ራ​ጥ​ስ​ንም ተሻ​ግሮ ወደ መስ​ጴ​ጦ​ምያ ሄደ፤ ወደ ባሕ​ርም እስ​ኪ​ደ​ርስ ድረስ በአ​ር​ባኒ ወን​ዞች ላይ ያሉ ታላ​ላቅ ከተ​ሞ​ችን ሁሉ አፈ​ረሰ።

25 የቂ​ል​ቅ​ያ​ንም አው​ራጃ ያዘ፤ ጠላ​ቱ​ንም ሁሉ አጠፋ፤ በም​ዕ​ራ​ብም አን​ጻር በዐ​ዜብ በኩል እስከ ያፌት አው​ራጃ ድረስ ሄደ።

26 የም​ድ​ያ​ም​ንም ልጆች ሁሉ ከበ​ባ​ቸው፤ ከብ​ታ​ቸ​ው​ንም ዘረፈ፤ ቤታ​ቸ​ው​ንም አቃ​ጠለ።

27 በስ​ንዴ አዝ​መራ ጊዜም በደ​ማ​ስቆ ወዳለ ሜዳ ወርዶ አዝ​መ​ራ​ቸ​ውን ሁሉ አቃ​ጠለ፤ የላ​ሞ​ቻ​ቸ​ው​ንና የበ​ጎ​ቻ​ቸ​ው​ንም መን​ጋ​ዎች ይዘ​ር​ፏ​ቸው ዘንድ አዘዘ፤ አም​ባ​ቸ​ው​ንም አፈ​ረሰ፤ ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ማረከ፥ ጎል​ማ​ሶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሁሉ በጦር ገደለ።

28 ከእ​ነ​ር​ሱም የተ​ነሣ መፍ​ራ​ትና ድን​ጋጤ በባ​ሕሩ ዳርቻ በጢ​ሮ​ስና በሲ​ዶና በሚ​ኖሩ፥ በአ​ቂ​ናና በሴ​ይ​ርም፥ በያ​ም​ኒ​ያም በሚ​ኖሩ ሰዎች ላይ ወደቀ። በአ​ስ​ቀ​ሎ​ናና በአ​ዛ​ጦ​ንም የሚ​ኖሩ ሰዎች ከርሱ መም​ጣት የተ​ነሣ ፈጽ​መው ፈሩ።

Síguenos en:



Anuncios