Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ዮዲት 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ዮዲት ከሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ጋር ያደ​ረ​ገ​ችው የመ​ጀ​መ​ሪያ ትው​ውቅ

1 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም አላት፥ “አንቺ ሴት እመኝ፤ ለዓ​ለሙ ሁሉ ንጉሥ ለና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ይገዛ ዘንድ ራሱን ወደ እርሱ በመ​ለሰ ሰው እኔ ክፉ ነገ​ርን አላ​ደ​ር​ግ​ምና ልቡ​ናሽ አይ​ፍ​ራ​ብሽ።

2 አሁ​ንም በአ​ንባ የሚ​ኖሩ እነ​ዚህ ወገ​ኖ​ችሽ የወ​ነ​ጀ​ሉን ባይ​ሆኑ ኖሮ በእ​ነ​ርሱ ላይ ጦሬን ባላ​ነ​ሣ​ሁም ነበር፤ ነገር ግን ይህን ነገር እነ​ርሱ አደ​ረ​ጉት።

3 አሁ​ንም ንገ​ሪኝ፤ ከእ​ነ​ርሱ ዘንድ ስለ​ምን ነገር ኰብ​ል​ለሽ ወደ እኛ መጣሽ? ነገር ግን ለሕ​ይ​ወ​ትሽ መጥ​ተ​ሻ​ልና በዚህ ሌሊት ለሁ​ል​ጊ​ዜም እን​ድ​ት​ድኚ እመኝ።

4 ለን​ጉሡ ለጌ​ታ​ችን ለና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር አሽ​ከ​ሮች እን​ደ​ም​ና​ደ​ርግ ላንቺ ከም​ና​ደ​ር​ገው በጎ ነገር በቀር በአ​ንቺ ክፉ ነገር የሚ​ያ​ደ​ርግ የለም።”

5 ዮዲ​ትም አለ​ችው፥ “የእ​ኔን የባ​ሪ​ያ​ህን ቃል ተቀ​በል፤ እኔ ባሪ​ያህ በፊ​ትህ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ በዚች ሌሊት እኔ ለጌ​ታዬ ሐሰት ነገ​ርን አል​ነ​ግ​ር​ህም።

6 የእ​ኔን የአ​ገ​ል​ጋ​ይ​ህን ቃል ከተ​ከ​ተ​ልህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለአ​ንተ ፍጹም ሥራ ይሠ​ራ​ል​ሃል፤ አንተ ጌታዬ ካሰ​ብ​ኸው ነገር የሚ​ወ​ድቅ የለም።

7 የም​ድር ሁሉ ንጉሥ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር በሕ​ይ​ወት ይኑር! ፍጥ​ረ​ቱን ሁሉ ታቀና ዘንድ አን​ተን የላከ ኀይሉ ይኑር። በም​ድረ በዳ የሚ​ኖሩ አው​ሬ​ዎ​ችና እን​ስሳ፥ በሰ​ማይ የሚ​በሩ ወፎ​ችም በኀ​ይ​ልህ ከና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርና ከቤቱ በታች ይኖ​ራሉ እንጂ በዘ​መ​ንህ ሰዎች ብቻ የሚ​ገ​ዙ​ለት አይ​ደ​ለም።

8 ሥራ​ህ​ንና የል​ቡ​ና​ህን ጥበብ ሰም​ተ​ና​ልና በመ​ን​ግ​ሥቱ ሁሉ አንተ ብቻ ቸር እንደ ሆንህ፥ በአ​ገሩ ሁሉ ተሰ​ም​ት​ዋ​ልና፥ በሥ​ራ​ህም ሁሉ አንተ ብርቱ ነህና፥ በሰ​ል​ፍ​ህም ሁሉ አንተ የተ​ደ​ነ​ቅህ ነህና።

9 “አሁ​ንም አክ​ዮር በጉ​ባ​ኤ​ያ​ችሁ የአ​ላ​ች​ሁን ነገር ሰማን፤ ለአ​ዳ​ኑት የቤ​ጤ​ልዋ ሰዎ​ችም ለአ​ንተ የነ​ገ​ረ​ህን ነገር ሁሉ ነገ​ራ​ቸው።

10 አቤቱ ጌታዬ፥ ነገ​ሩን አት​ናቅ፤ ነገር ግን እው​ነት ስለ​ሆነ በል​ብህ አኑ​ረው፤ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ካል​በ​ደሉ ሕዝ​ባ​ችን ሊጠፉ አይ​ች​ሉም፤ ሰይ​ፍም ሊያ​ጠ​ፋ​ቸው አይ​ች​ልም።

11 አሁ​ንም ጌታዬ የተ​ና​ቀና የማ​ይ​ረባ እን​ዳ​ይ​ሆን በፊ​ትህ ሞታ​ቸው ይደ​ር​ስ​ባ​ቸው ዘንድ በበ​ደ​ላ​ቸው ሥራ አም​ላ​ካ​ቸ​ውን ያሳ​ዘ​ኑ​ባት ኀጢ​አ​ታ​ቸው በዚህ ታገ​ኛ​ቸ​ዋ​ለች።

12 እህ​ላ​ቸ​ውና ውኃ​ቸው አል​ቋ​ልና፥ ከብ​ታ​ቸ​ው​ንም ይበሉ ዘንድ ተመ​ል​ሰ​ዋ​ልና፥ እን​ዳ​ይ​በሉ አም​ላ​ካ​ቸው በኦ​ሪ​ታ​ቸው የከ​ለ​ከ​ላ​ቸ​ውን ያን ይበሉ ዘንድ ደር​ሰ​ዋ​ልና።

13 የእ​ህ​ላ​ቸ​ውን መጀ​መ​ሪ​ያና የወ​ይ​ና​ቸ​ውን ዐሥ​ራት በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ችን ፊት በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ለሚ​ቆሙ ለካ​ህ​ናት የለ​ዩ​ትን፥ ከሕ​ዝ​ቡም ላንድ ሰው ስንኳ በእ​ጃ​ቸው መዳ​ሰስ የማ​ይ​ገ​ባ​ቸ​ውን ይህን ዘይ​ቱ​ንም ሊበሉ አስ​በ​ዋ​ልና፥

14 ከአ​ለ​ቆ​ችም ፈቃድ ያመ​ጡ​ላ​ቸው ዘንድ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ላኩ፤ በዚያ የሚ​ኖሩ ሰዎች እን​ዲህ አድ​ር​ገ​ዋ​ልና።

15 ፈቃ​ዱን ከነ​ገ​ሩ​አ​ቸ​ውና እን​ዲህ ከአ​ደ​ረጉ በኋላ እን​ዲህ አድ​ር​ገ​ዋ​ልና በዚያ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእ​ጅህ ይጥ​ላ​ቸ​ዋል።

16 “እኔ ባር​ያህ ይህን ሁሉ በዐ​ወ​ቅሁ ጊዜ ከእ​ነ​ርሱ ኰበ​ለ​ልሁ፤ የሰ​ማ​ውን ሰው​ንና ምድ​ርን ሁሉ የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግጥ ይህን ሥራ ከአ​ንተ ጋር እሠራ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ላከኝ።

17 እኔ አገ​ል​ጋ​ይህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ፈራ ነኝና የሰ​ማይ አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም በመ​ዓ​ል​ትና በሌ​ሊት አገ​ለ​ግ​ለ​ዋ​ለሁ። አቤቱ፥ አሁ​ንም ከአ​ንተ ጋር እኖ​ራ​ለሁ፤ ነገር ግን እኔ አገ​ል​ጋ​ይህ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እለ​ምን ዘንድ ሌሊት ወደ ምድረ በዳ እወ​ጣ​ለሁ፤ መቼም የሠ​ሩ​ትን ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ይነ​ግ​ረ​ኛል።

18 መጥ​ቼም ይህን እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ ከሠ​ራ​ዊ​ትህ ሁሉ ጋር ትወ​ጣ​ለህ፤ የሚ​ቃ​ወ​ም​ህም አይ​ኖ​ርም።

19 ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም እስ​ክ​ት​ደ​ር​ስም ድረስ በይ​ሁዳ መካ​ከል እወ​ስ​ድ​ሃ​ለሁ፤ በመ​ካ​ከ​ሏም ዙፋ​ን​ህን ትዘ​ረ​ጋ​ለህ እረ​ኛ​ቸ​ውም እንደ በተ​ና​ቸው በጎች ፈጽ​መህ ትከ​ብ​ባ​ቸ​ዋ​ለህ፤ ውሻም በፊ​ትህ አይ​ጮ​ህ​ብ​ህም። ለእኔ እን​ዲህ ተነ​ግ​ሮ​ኛ​ልና። ይህ​ንም ዐውቄ እነ​ግ​ርህ ዘንድ ተላ​ክሁ።”

20 ነገ​ሯም ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስ​ንና ሰዎ​ቹን ሁሉ ደስ አሰ​ኛ​ቸው። እነ​ር​ሱም ጥበ​ቧን አደ​ነቁ።

21 እን​ዲ​ህም አሉ፥ “ከም​ድር ዳርቻ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ በፊቷ ደም ግባ​ትና በቃ​ልዋ ጥበብ እን​ደ​ዚች ሴት ያለ የለም።”

22 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም አላት፥ “ኀይል በእ​ጃ​ችን፥ ጥፋ​ትም ጌታ​ዬን በካ​ዱት ላይ ይሆን ዘንድ ከሕ​ዝ​ብሽ አስ​ቀ​ድሞ የላ​ከሽ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጎ ነገ​ርን አደ​ረገ።

23 አሁ​ንም አንቺ በመ​ል​ክሽ ውብ ነሽ፤ በቃ​ል​ሽም የተ​ባ​ረ​ክሽ ነሽ፤ እን​ዳ​ል​ሽ​ውም ከአ​ደ​ረ​ግሽ አም​ላ​ክሽ አም​ላኬ ይሆ​ነ​ኛል፤ አን​ቺም በን​ጉሡ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ቤተ መን​ግ​ሥት ትኖ​ሪ​ያ​ለሽ፤ ስም​ሽም በሀ​ገሩ ሁሉ ከፍ ከፍ ይላል።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos