Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ዮዲት 10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ዮዲት ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ለመ​ሄድ እንደ ተዘ​ጋ​ጀች

1 ከዚ​ህም በኋላ ወደ እስ​ራ​ኤል አም​ላክ መለ​መ​ኗን ከጨ​ረ​ሰ​ችና ይህ​ንም ነገር ሁሉ ከፈ​ጸ​መች በኋላ፥

2 ከወ​ደ​ቀ​ች​በት ቦታ ተነ​ሣች፤ ብላ​ቴ​ና​ዋ​ንም ጠርታ በሰ​ን​በ​ታ​ትና በበ​ዓ​ላት ቀኖች ወደ​ም​ት​ቀ​መ​ጥ​በት ቤትዋ ወረ​ደች።

3 የለ​በ​ሰ​ች​ው​ንም ማቅ አወ​ለ​ቀች፤ የመ​በ​ለ​ት​ነ​ት​ዋ​ንም ልብስ ለበ​ሰች፥ ሰው​ነ​ት​ዋ​ንም በውኃ ታጠ​በች፤ ጠጕ​ር​ዋ​ንም ያማረ ሽቱ ተቀ​ባች፤ ጠጕ​ር​ዋ​ንም ተሠ​ራች፤ አጌ​ጠ​ችም፤ ከዚ​ህም በኋላ ባሏ ምናሴ በሕ​ይ​ወት በነ​በረ ጊዜ የም​ት​ለ​ብ​ሰ​ውን የደ​ስታ ልብ​ሷን ለበ​ሰች።

4 ጫማ​ዋ​ንም ተጫ​ማች፤ አል​ቦ​ዋ​ንና ቀለ​በ​ት​ዋን፥ አም​ባ​ር​ዋ​ንና ጉት​ቻ​ዋ​ንም አደ​ረ​ገች፤ ጌጡ​ንም ሁሉ አጌ​ጠች፤ የሚ​ያ​ዩ​አ​ት​ንም ወን​ዶች ሁሉ ዐይን እስ​ክ​ታ​ስት ድረስ ፈጽማ አጌ​ጠች።

5 የወ​ይ​ኑን ገን​ቦና የዘ​ይ​ቱን ማሰሮ ትሸ​ከም ዘንድ ለብ​ላ​ቴ​ናዋ ሰጠ​ቻት፤ ስልቅ በሶ​ውን፥ የስ​ንዴ አም​ባ​ሻ​ው​ንና በለ​ሱን በስ​ል​ቻዋ መላች፤ ገን​ዘ​ብ​ዋ​ንም ሁሉ አን​ግታ አሸ​ከ​መ​ቻት።

6 ወደ ቤጤ​ልዋ ከተማ በርም ሄደች፤ ዖዝ​ያ​ንን፥ ያገር ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችን ከር​ሚ​ንና ከብ​ሪ​ም​ንም በዚያ ቆመው አገ​ኘ​ቻ​ቸው።

7 ፊትዋ ተለ​ውጦ፥ በሚ​ያ​ስ​ደ​ንቅ ሁኔታ ልብ​ሷን ለብሳ ባዩ​አት ጊዜ ከደም ግባቷ ማማር የተ​ነሣ እጅግ ተደ​ነቁ፤ እን​ዲ​ህም አሏት፦

8 “ለኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ልዕ​ል​ናና ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ክብር በል​ብሽ ያሰ​ብ​ሽ​ውን ታደ​ርጊ ዘንድ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን አም​ላክ ሞገ​ስን ይስ​ጥሽ።” እር​ሷም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰገ​ደች።

9 እን​ዲ​ህም አለ​ቻ​ቸው፥ “አሁ​ንም ከእ​ና​ንተ ጋራ የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ት​ን​ነ​ገር ወጥቼ አደ​ርግ ዘንድ የከ​ተ​ማ​ውን በር የሚ​ከ​ፍ​ት​ልኝ ሰው እዘ​ዙ​ልኝ፤” እንደ ጠየ​ቀ​ችም ይከ​ፍ​ቱ​ላት ዘንድ ጐል​ማ​ሶ​ችን አዘ​ዙ​አ​ቸው።

10 ይህ​ንም በአ​ደ​ረጉ ጊዜ ዮዲት ወጣች፤ ብላ​ቴ​ና​ዋም ከእ​ርሷ ጋር ወጣች፤ የከ​ተ​ማው ሰዎ​ችም ካን​ባው ወርዳ ከሸ​ለ​ቆው እስ​ክ​ታ​ልፍ ድረስ ያዩ​አት ነበር፤ ከዚህ በኋላ ግን አላ​ዩ​አ​ትም።

11 በቀ​ጥ​ታም በሸ​ለ​ቆው ሄደች፤ የአ​ሦ​ራ​ው​ያ​ንም ዘበ​ኞች አገ​ኙ​አት።

12 ይዘ​ውም መረ​መ​ሩ​አት፤ እን​ዲ​ህም አሏት፥ “አንቺ ማን ነሽ? ከየት መጣሽ? ወዴ​ትስ ትሄ​ጃ​ለሽ?” እር​ስ​ዋም አለ​ቻ​ቸው፥ “እኔ ከዕ​ብ​ራ​ው​ያን የተ​ወ​ለ​ድሁ ነኝ፤ ሀገ​ራ​ቸ​ውን ለእ​ና​ንተ አሳ​ል​ፈው ሊሰጡ በወ​ደዱ ጊዜ ከእ​ነ​ርሱ ኰብ​ልዬ መጣሁ።

13 እኔ እው​ነ​ተኛ ነገ​ርን እነ​ግ​ረው ዘንድ፥ የም​ት​ሄ​ዱ​በ​ት​ንም ጎዳና አሳ​የው ዘንድ ወደ ቢት​ወ​ደ​ዳ​ችሁ ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ አስ​ቀ​ድሜ መጣሁ፤ አው​ራ​ጃ​ቸ​ው​ንም ሁሉ ገን​ዘብ ታደ​ር​ጋ​ላ​ችሁ፤ ከሰ​ዎ​ቻ​ችሁ አንድ ሰው ስንኳ የሚ​ቈ​ስል የለም።”

14 እነ​ዚ​ያም ሰዎች ቃል​ዋን በሰሙ ጊዜ፥ ፊት​ዋ​ንም ባዩ ጊዜ፥ ደም ግባ​ት​ዋም ፈጽሞ የተ​ደ​ነቀ እንደ ሆነ ባዩ ጊዜ እን​ዲህ አሏት፦

15 “ወደ ጌታ​ችን ፈጥ​ነሽ የወ​ረ​ድሽ አንቺ ሕይ​ወ​ት​ሽን አዳ​ንሽ። አሁ​ንም ወደ ድን​ኳኑ ሂጂ፤ ወደ እርሱ የሚ​ያ​ደ​ር​ስ​ሽን ሰው ከእኛ እን​ል​ካ​ለን።

16 በፊ​ቱም በቆ​ምሽ ጊዜ ይህን ነገ​ር​ሽን ንገ​ሪው እንጂ ልቡ​ናሽ አይ​ፍራ፤ በጎ ነገ​ርን ያደ​ር​ግ​ል​ሻል።”

17 ከእ​ር​ስ​ዋና ከብ​ላ​ቴ​ናዋ ጋር የሚ​ሄዱ አንድ መቶ ሰዎ​ችን መረጡ፤ ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ድን​ኳ​ንም አደ​ረ​ሷት።

18 ሕዝ​ቡም ሁሉ ተሰ​በ​ሰቡ፤ በድ​ን​ኳኑ ፊት እን​ዳ​ለች ዜናዋ በሰ​ፈሩ ተሰ​ምቶ ነበ​ርና መጥ​ተው ስለ እርሷ እስ​ኪ​ነ​ግ​ሩት ድረስ ከሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ድን​ኳን ውጭ ከብ​በ​ዋት ቆሙ።

19 ደም ግባ​ት​ዋ​ንም አደ​ነቁ፤ ስለ እር​ስ​ዋም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች አደ​ነቁ፤ እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም፥ “እንደ እነ​ዚህ ያሉ ሴቶች ያሉ​ትን ሕዝብ የሚ​ንቅ ማን ነው? ዓለ​ሙን ሁሉ ሊተ​ነ​ኰሉ ስለ​ሚ​ችሉ ከእ​ነ​ዚህ ሰዎች አንድ ሰውስ እንኳ ይቀር ዘንድ መል​ካም አይ​ደ​ለም” ተባ​ባሉ።

20 በሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ አጠ​ገብ የተ​ቀ​መጡ አሽ​ከ​ሮ​ቹም ሁሉ መጥ​ተው ወደ ድን​ኳኑ አገ​ቧት።

21 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም በወ​ርቅ፥ በመ​ረ​ግ​ድና ዋጋው ብዙ በሆነ ዕንቍ የተ​ሠራ ነጭ ሐር በተ​ነ​ጠ​ፈ​በት በዙ​ፋኑ ላይ በድ​ን​ኳኑ ውስጥ ተኝቶ ነበር።

22 የእ​ር​ሷ​ንም ነገር ነገ​ሩት፤ ወደ አደ​ባ​ባ​ይም ወጣ፤ በፊ​ቱም የብር መቅ​ረዝ ፋና ይበራ ነበር።

23 ዮዲ​ትም ወደ እርሱ በቀ​ረ​በች ጊዜ አሽ​ከ​ሮቹ ቆመው ነበር፤ ከመ​ልኳ ደም ግባት የተ​ነሣ ሁሉም ተደ​ነቁ፤ እር​ሷም በግ​ን​ባሯ በም​ድር ላይ ወድቃ ሰገ​ደ​ች​ለት፤ አሽ​ከ​ሮ​ቹም አነ​ሡ​አት።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos