Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ዮዲት 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ንጉሥ አር​ፋ​ክ​ስድ የባ​ጥ​ናን ዙሪያ እንደ ቀጸረ

1 በታ​ላ​ቅዋ ከተማ በነ​ነዌ ለአ​ሦር በነ​ገሠ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር በዐ​ሥራ ሁለ​ተ​ኛው ዓመት፥ ሜዶ​ን​ንና ባጥ​ናን ይገዛ የነ​በ​ረው ንጉሥ አር​ፋ​ክ​ስድ፥

2 የባ​ጥ​ናን ዙሪያ በለ​ዘበ ድን​ጋይ ሠራ፤ በከ​ተ​ማዋ ወርድ በኩል የመ​ሠ​ረ​ትዋ ስፋት ሠላሳ ክንድ ነው፤ በከ​ተ​ማዋ ፊት ለፊት ያለው ስፋት ስድሳ ክንድ ርዝ​መት ነው። የግ​ን​ቡን ቁመት ሰባ ክንድ አድ​ርጎ ሠራ፤ ማዕ​ዘ​ኑም አምሳ ክንድ ነው።

3 በየ​በሩ መቶ መቶ ክንድ እያ​ለፈ የጕ​በኛ ቤቱን አቆመ፤ መሠ​ረ​ቱም ከማ​ዕ​ዘን እስከ ማዕ​ዘን ድረስ ስድሳ ክንድ ነው።

4 ጽኑ​ዓኑ፥ ኀያ​ላ​ኑና የጥ​በቃ ሠራ​ዊቱ የሚ​ገ​ቡ​ባ​ቸው የሚ​ከ​ፈቱ የበ​ሮ​ች​ዋን ደጃፍ ቁመ​ታ​ቸ​ውን ሰባ ክንድ፥ ስፋ​ታ​ቸ​ውን አርባ ክንድ አድ​ርጎ ሠራ።

5 በዚ​ያም ወራት ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ንጉሡ አር​ፋ​ስ​ክ​ድን በሰፊ ሜዳ ተዋ​ጋው፤ ያም ሜዳ በራ​ግው አው​ራጃ ያለ ነው።

6 በአ​ምባ የሚ​ኖሩ ሰዎ​ችም ሁሉ ወጥ​ተው ተቀ​በ​ሉት፤ በኤ​ፍ​ራ​ጥ​ስና በጤ​ግ​ሮስ፥ በሒ​ደ​ስ​ጶ​ንም፥ በኤ​ሊ​ሜ​ዎን ንጉሥ በአ​ር​ዮክ ግዛት አው​ራጃ ያሉ ሁሉ የካ​ሉ​ድን ልጆች ይዋ​ጓ​ቸው ዘንድ እጅግ ብዙ የሆኑ አሕ​ዛ​ብም ተሰ​በ​ሰቡ።

7 የፋ​ርስ ንጉሥ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርም በፋ​ርስ አው​ራጃ ለሚ​ኖሩ ሁሉ፥ በቂ​ል​ቅያ፥ በደ​ማ​ስ​ቆና በሊ​ባ​ኖስ ምዕ​ራብ ወደ​ሚ​ኖሩ ሁሉ በወ​ንዝ ዳርም ወደ​ሚ​ኖሩ ሰዎች ሁሉ ላከ።

8 በቀ​ር​ሜ​ሎ​ስና በገ​ለ​ዓድ፥ በገ​ሊ​ላና ሰፊ በሆነ በአ​ስ​ዴ​ራን ምድረ በዳ ለሚ​ኖሩ አሕ​ዛብ።

9 በሰ​ማ​ር​ያና በአ​ው​ራ​ጃዋ ለሚ​ኖሩ ሰዎች ሁሉ፥ በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ እስከ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና እስከ ቢላ​ጢኒ፥ እስከ ኪሎ​ስና እስከ ቃዴስ እስከ ግብፅ ወንዝ፥ ጣፍ​ና​ስና ራሚስ እስከ ጌሴም ምድር ሁሉ።

10 በጣ​ኔ​ዎ​ስና በሜ​ኒ​ፌ​ዎስ በላይ እስ​ኪ​ደ​ርስ በግ​ብፅ ለሚ​ኖሩ ሁሉ እስከ ኢት​ዮ​ጵያ ድን​በር ድረስ ሁሉ ላከ።

11 በም​ድር የሚ​ኖሩ ሁሉ የፋ​ርስ ንጉሥ የና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርን ትእ​ዛዝ እንቢ አሉ፤ ከእ​ር​ሱም ጋር ወደ ጦር አል​ሄ​ዱም። አል​ፈ​ሩ​ት​ምና በፊ​ታ​ቸው እንደ አንድ ሰው ሆኗ​ልና። መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ቹም ባዶ​አ​ቸ​ውን በው​ር​ደት ከፊ​ታ​ቸው ተመ​ለሱ።

12 ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርም በዚ​ያች ምድር ላይ ፈጽሞ ተቈጣ፤ የቂ​ል​ቅ​ያ​ንና የደ​ማ​ስ​ቂ​ኒ​ስን፥ የሶ​ር​ያ​ንም አው​ራጃ ሁሉ ይበ​ቀ​ልና በሞ​ዓብ ምድር የሚ​ኖ​ሩ​ትን ሁሉ፥ የአ​ሞ​ን​ንም ልጆች ይሁ​ዳ​ንም ሁሉ በግ​ብፅ የሚ​ኖ​ሩ​ት​ንም ከሁ​ለቱ ባሕ​ሮች ድረስ ተበ​ቅሎ በሰ​ይፍ ያጠ​ፋ​ቸው ዘንድ በዙ​ፋ​ኑና በመ​ን​ግ​ሥቱ ማለ።


ንጉሥ አር​ፋ​ክ​ስድ ድል እንደ ሆነ

13 ከሠ​ራ​ዊቱ ሁሉ ጋር ንጉሡ አር​ፋ​ክ​ስ​ድን በነ​ገሠ በዐ​ሥራ ሰባ​ተ​ኛው ዓመት ተዋ​ጋው፤ ድል ነሥ​ቶም የአ​ር​ፋ​ክ​ስ​ድን ሠራ​ዊ​ቱን ሁሉ፥ ፈረ​ሶ​ቹ​ንና ሰረ​ገ​ላ​ዎ​ቹን ሁሉ ወሰደ።

14 ሀገ​ሮ​ቹ​ንም ሁሉ ያዘ፤ እስከ ባጥ​ናም ድረስ ሄዶ አም​ባ​ቸ​ውን ያዘ፤ ሀገ​ሩ​ንም ሁሉ በረ​በረ፤ አጠ​ፋ​ትም።

15 አር​ፋ​ክ​ስ​ድ​ንም በራ​ግው አው​ራጃ ይዞ በጦር ወጋው፤ ፈጽ​ሞም አጠ​ፋው።

16 እር​ሱም ተመ​ለሰ፤ ከእ​ርሱ ጋር ያሉ እጅግ አር​በ​ኞች የሆኑ ብዙ ሰዎ​ችም ሁሉ ተመ​ለሱ፤ በዚ​ያም ሲያ​ስ​ብና ሲመ​ክር መቶ ሃያ ቀን ተቀ​መጠ።

Síguenos en:



Anuncios