Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዮሐንስ 18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ይሁዳ ጌታ​ች​ንን አሳ​ልፎ ስለ መስ​ጠቱ

1 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም ይህን ተና​ግሮ አት​ክ​ልት ወደ አለ​በት ስፍራ ወደ ቄድ​ሮስ ወንዝ ማዶ ከደቀ መዛ​ሙ​ርቱ ጋር ወጣ፤ ከደቀ መዛ​ሙ​ር​ቱም ጋር ወደ​ዚያ ገባ።

2 አሳ​ልፎ የሚ​ሰ​ጠው ይሁ​ዳም ያን ስፍራ ያው​ቀው ነበር፤ ጌታ​ችን ኢየ​ሱስ ከደቀ መዛ​ሙ​ርቱ ጋር ወደ​ዚያ ብዙ ጊዜ ይሄድ ነበ​ርና።

3 ይሁ​ዳም ከካ​ህ​ናት አለ​ቆ​ችና ከፈ​ሪ​ሳ​ው​ያን ወታ​ደ​ሮ​ችን ተቀ​በለ፤ ሎሌ​ዎ​ቻ​ቸ​ው​ንም በረ​ዳ​ት​ነት ወሰደ፤ ፋኖ​ስና የችቦ መብ​ራት፥ የጦር መሣ​ሪ​ያም ይዞ ወደ​ዚያ ሄደ።

4 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም የሚ​ደ​ር​ስ​በ​ትን ሁሉ ዐውቆ ወደ እነ​ርሱ ወደ ውጭ ወጣና፥ “ማንን ትሻ​ላ​ችሁ?” አላ​ቸው።

5 “የና​ዝ​ሬ​ቱን ኢየ​ሱ​ስን” ብለው መለ​ሱ​ለት፤ ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም፥ “እኔ ነኝ” አላ​ቸው፤ አሳ​ልፎ የሰ​ጠው ይሁ​ዳም በዚ​ያው አብ​ሮ​አ​ቸው ቆሞ ነበር።

6 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም፥ “እኔ ነኝ” ባላ​ቸው ጊዜ፤ ወደ ኋላ​ቸው ተመ​ል​ሰው በም​ድር ላይ ወደቁ።

7 ከዚ​ህም በኋላ እን​ደ​ገና፥ “ማንን ትሻ​ላ​ችሁ?” ብሎ ጠየ​ቃ​ቸው፤ እነ​ር​ሱም፥ “የና​ዝ​ሬ​ቱን ኢየ​ሱ​ስን” አሉት።

8 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም፥ “እኔ ነኝ አል​ኋ​ችሁ፤ እኔን የም​ትሹ ከሆነ እነ​ዚ​ህን ተዉ​አ​ቸው፤ ይሂዱ” አላ​ቸው።

9 ይህም፥ “ከእ​ነ​ዚህ ከሰ​ጠ​ኸኝ አንድ ስንኳ አል​ጠ​ፋም” ያለው ቃሉ ይፈ​ጸም ዘንድ ነው።

10 ስም​ዖን ጴጥ​ሮ​ስም ሾተል ነበ​ረው፤ ሾተ​ሉ​ንም መዝዞ የሊቀ ካህ​ና​ቱን አገ​ል​ጋይ መትቶ ቀኝ ጆሮ​ውን ቈረ​ጠው፤ የዚ​ህም አገ​ል​ጋይ ስም ማል​ኮስ ይባል ነበር።

11 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም ጴጥ​ሮ​ስን፥ “ሾተ​ል​ህን ወደ አፎቷ መልስ፤ አብ የሰ​ጠ​ኝን ጽዋ ሳል​ጠጣ እተ​ወ​ዋ​ለ​ሁን?” አለው።


ወደ ሊቃነ ካህ​ናት ስለ መሄዱ

12 ጭፍ​ሮ​ችና የሺ አለ​ቃው፥ የአ​ይ​ሁ​ድም ሎሌ​ዎች ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን ይዘው አሰ​ሩት።

13 አስ​ቀ​ድ​ሞም ወደ ሐና ወሰ​ዱት፤ በዚ​ያች ዓመት የካ​ህ​ናት አለቃ ለነ​በ​ረው ለቀ​ያፋ አማቱ ነበ​ርና።

14 ቀያ​ፋም “ስለ ሕዝቡ ሁሉ አንድ ሰው ቢሞት ይሻ​ላል” ብሎ አይ​ሁ​ድን የመ​ከ​ራ​ቸው ነበር።


ስለ ጴጥ​ሮስ ክህ​ደት

15 ስም​ዖን ጴጥ​ሮ​ስና ሌላው ደቀ መዝ​ሙ​ርም ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን ከሩቅ ተከ​ተ​ሉት፤ ያ ደቀ መዝ​ሙር ግን በሊቀ ካህ​ናቱ ዘንድ የታ​ወቀ ነበር፤ ከጌ​ታ​ችን ኢየ​ሱስ ጋርም ወደ ሊቀ ካህ​ናቱ ግቢ ገባ።

16 ጴጥ​ሮስ ግን በስ​ተ​ውጭ በበሩ ቆሞ ነበር፤ ያም በሊቀ ካህ​ናቱ ዘንድ ይታ​ወቅ የነ​በ​ረው ሌላው ደቀ መዝ​ሙር ወጣና ለበ​ረ​ኛ​ዪቱ ነግሮ ጴጥ​ሮ​ስን አስ​ገ​ባው።

17 በረ​ኛ​ዪቱ አገ​ል​ጋ​ይም፥ “አን​ተም ከዚያ ሰው ደቀ መዛ​ሙ​ርት ወገን አይ​ደ​ለ​ህ​ምን?” አለ​ችው፤ እር​ሱም፥ “አይ​ደ​ለ​ሁም” አላት።

18 አገ​ል​ጋ​ዮ​ችና ሎሌ​ዎ​ችም በዚያ ቆመው እሳት አን​ድ​ደው ይሞቁ ነበር፤ የዚ​ያች ሌሊት ብርድ ጽኑ ነበ​ርና፤ ጴጥ​ሮ​ስም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ቆሞ ይሞቅ ነበረ።


ሊቀ ካህ​ናቱ እንደ ጠየ​ቀው

19 ሊቀ ካህ​ና​ቱም ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን፦ ስለ ደቀ መዛ​ሙ​ር​ቱና ስለ ትም​ህ​ርቱ ጠየ​ቀው።

20 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም መልሶ እን​ዲህ አለው፥ “እኔ ለዓ​ለም በግ​ልጥ ተና​ገ​ርሁ፤ አይ​ሁድ ሁሉ በሚ​ሰ​በ​ሰ​ቡ​በት በም​ኵ​ራ​ብም፥ በቤተ መቅ​ደ​ስም ሁል​ጊዜ አስ​ተ​ማ​ርሁ፤ በስ​ው​ርም የተ​ና​ገ​ር​ሁት አን​ዳች ነገር የለም።

21 እን​ግ​ዲህ እኔን ለምን ትጠ​ይ​ቀ​ኛ​ለህ? የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ትን የሰ​ሙ​ኝን ጠይ​ቃ​ቸው፤ እኔም የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ትን እነሆ፥ እነ​ርሱ ያው​ቃሉ።”

22 ይህ​ንም ባለ​ጊዜ ከቆ​ሙት ሎሌ​ዎች አንዱ፥ “ለሊቀ ካህ​ናቱ እን​ዲህ ትመ​ል​ስ​ለ​ታ​ለ​ህን?” ብሎ ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን በጥፊ መታው።

23 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም መልሶ፥ “ክፉ ተና​ግሬ እንደ ሆንሁ ስለ ክፉ መስ​ክ​ር​ብኝ፤ መል​ካም ተና​ግሬ እንደ ሆንሁ ግን ለምን ትመ​ታ​ኛ​ለህ?” አለው።

24 ሐናም ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን እንደ ታሰረ ወደ ሊቀ ካህ​ናቱ ወደ ቀያፋ ላከው።

25 ስም​ዖን ጴጥ​ሮ​ስም ቆሞ እሳት ይሞቅ ነበር፤ “አን​ተስ ከእ​ርሱ ደቀ መዛ​ሙ​ርት ወገን አይ​ደ​ለ​ህ​ምን?” አሉት፤ እር​ሱም፥ “አይ​ደ​ለ​ሁም” ብሎ ካደ።

26 ጴጥ​ሮስ ጆሮ​ውን ከቈ​ረ​ጠው ሰው ዘመ​ዶች ወገን የሆነ ከሊቀ ካህ​ናቱ አገ​ል​ጋ​ዮ​ችም አንድ ሰው፥ “እኔ በአ​ት​ክ​ልት ቦታ ውስጥ ከእ​ርሱ ጋር አይ​ችህ አል​ነ​በ​ረ​ምን?” አለው።

27 ጴጥ​ሮ​ስም ደግሞ ካደ፤ ያን​ጊ​ዜም ዶሮ ጮኸ።


ጌታ በጲ​ላ​ጦስ ፊት ስለ መቆሙ

28 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስ​ንም ከቀ​ያፋ ወደ ፍርድ አደ​ባ​ባይ ወሰ​ዱት፤ አይ​ሁድ ግን ፈጽሞ ስለ ነጋ የፋ​ሲ​ካ​ውን በግ ሳይ​በሉ እን​ዳ​ይ​ረ​ክሱ ወደ ፍርድ አደ​ባ​ባይ አል​ገ​ቡም።

29 ጲላ​ጦ​ስም ወደ እነ​ርሱ ወደ ውጭ ወጥቶ፥ “ይህን ሰው ወደ እኔ ያመ​ጣ​ች​ሁ​በት በደሉ ምን​ድ​ነው?” አላ​ቸው።

30 እነ​ር​ሱም፥ “ክፉ የሠራ ባይ​ሆ​ንስ ወደ አንተ አሳ​ል​ፈን ባል​ሰ​ጠ​ነው ነበር” ብለው መለ​ሱ​ለት።

31 ጲላ​ጦ​ስም፥ “እና​ንተ ወስ​ዳ​ችሁ እንደ ሕጋ​ችሁ ፍረ​ዱ​በት” አላ​ቸው፤ አይ​ሁ​ድም፥ “እኛስ ማን​ንም ልን​ገ​ድል አል​ተ​ፈ​ቀ​ደ​ል​ንም” አሉት።

32 ይህም በምን ዐይ​ነት ሞት ይሞት ዘንድ እን​ዳ​ለው ሲያ​መ​ለ​ክት የተ​ና​ገ​ረው የጌ​ታ​ችን የኢ​የ​ሱስ ቃል ይፈ​ጸም ዘንድ ነው።

33 ጲላ​ጦ​ስም እን​ደ​ገና ወደ ፍርድ አደ​ባ​ባይ ገብቶ ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስን ጠራና፥ “የአ​ይ​ሁድ ንጉሥ አንተ ነህን?” አለው።

34 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም፥ “ይህን የም​ት​ና​ገር ከራ​ስህ ነውን? ወይስ ስለ እኔ የነ​ገ​ረህ ሌላ አለን?” ብሎ መለ​ሰ​ለት።

35 ጲላ​ጦ​ስም መልሶ፥ “እኔ አይ​ሁ​ዳዊ ነኝን? ለእኔ አሳ​ል​ፈው የሰ​ጡህ ወገ​ኖ​ች​ህና ሊቃነ ካህ​ናት አይ​ደ​ሉ​ምን? Aረ ምን አድ​ር​ገ​ሃል?” አለው።

36 ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም፥ “የእኔ መን​ግ​ሥት ከዚህ ዓለም አይ​ደ​ለ​ችም፤ መን​ግ​ሥ​ቴስ በዚህ ዓለም ብት​ሆን ኖሮ ለአ​ይ​ሁድ እን​ዳ​ል​ሰጥ አሽ​ከ​ሮች በተ​ዋ​ጉ​ልኝ ነበር፤ አሁ​ንም መን​ግ​ሥቴ ከዚህ አይ​ደ​ለ​ችም” ብሎ መለ​ሰ​ለት።

37 ጲላ​ጦ​ስም፥ “እን​ግ​ዲያ አንተ ንጉሥ ነህን?” አለው፤ ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም መልሶ፥ “እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ራስህ ትላ​ለህ፤ እኔ ስለ​ዚህ ተወ​ለ​ድሁ፤ ስለ​ዚ​ህም ለእ​ው​ነት ልመ​ሰ​ክር ወደ ዓለም መጣሁ፤ ከእ​ው​ነት የሆነ ሁሉ ቃሌን ይሰ​ማ​ኛል” አለው።

38 ጲላ​ጦ​ስም፥ “እው​ነት ምን​ድ​ነው?” አለው፤ ይህ​ንም ተና​ግሮ ዳግ​መኛ ወደ አይ​ሁድ ወጣና እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “እኔ አን​ዲት ስን​ኳን በደል አላ​ገ​ኘ​ሁ​በ​ትም።

39 ነገር ግን በየ​ዓ​መቱ በፋ​ሲካ በዓል ከእ​ስ​ረ​ኞች አንድ እን​ድ​ፈ​ታ​ላ​ችሁ ልማድ አላ​ችሁ፤ እን​ግ​ዲህ የአ​ይ​ሁ​ድን ንጉሥ ልፈ​ታ​ላ​ችሁ ትወ​ዳ​ላ​ች​ሁን?” አላ​ቸው።

40 ዳግ​መ​ኛም ድም​ፃ​ቸ​ውን ከፍ አድ​ር​ገው፥ “በር​ባ​ንን እንጂ ይህን አይ​ደ​ለም፤” አሉ፤ በር​ባን ግን ወን​በዴ ነበር።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos