Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዘፍጥረት 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የሰ​ና​ዖር ግንብ

1 የዓ​ለም ሁሉ ቋንቋ አንድ፥ ንግ​ግ​ሩም አንድ ነበረ።

2 እን​ዲ​ህም ሆነ፤ ከም​ሥ​ራ​ቅም ተነ​ሥ​ተው በሄዱ ጊዜ በሰ​ና​ዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚ​ያም ተቀ​መጡ።

3 እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም፥ “ኑ ጡብ እን​ሥራ፤ በእ​ሳ​ትም እን​ተ​ኵ​ሰው” ተባ​ባሉ። ጡባ​ቸ​ውም እንደ ድን​ጋይ፥ ጭቃ​ቸ​ውም እንደ ዝፍት ሆነ​ላ​ቸው።

4 እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም፥ “ኑ ለእኛ ከተ​ማና ራሱ ወደ ሰማይ የሚ​ደ​ርስ ግንብ እን​ሥራ፤ በም​ድር ፊት ሁሉ ላይ ሳን​በ​ተን ስማ​ች​ንን እና​ስ​ጠ​ራው” ተባ​ባሉ።

5 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሰ​ዎች ልጆች የሠ​ሩ​ትን ከተ​ማና ግንብ ለማ​የት ወረደ።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለ፥ “እነሆ፥ እነ​ርሱ አንድ ወገን ናቸው፤ ለሁ​ሉም አንድ ቋንቋ አላ​ቸው፤ ይህ​ንም ለማ​ድ​ረግ ጀመሩ፤ አሁ​ንም ያሰ​ቡ​ትን ሁሉ መሥ​ራ​ትን አይ​ተ​ዉም።

7 ኑ እን​ው​ረድ፤ አንዱ የሌ​ላ​ውን ነገር እን​ዳ​ይ​ሰ​ማው ቋን​ቋ​ቸ​ውን በዚያ እን​ደ​ባ​ል​ቀው።”

8 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቋን​ቋ​ቸ​ውን ለያየ፤ ከዚ​ያም በም​ድር ፊት ሁሉ ላይ በተ​ና​ቸው፤ ከዚ​ያም በኋላ ከተ​ማ​ዪ​ቱ​ንና ግን​ቡን መሥ​ራ​ትን ተዉ።

9 ስለ​ዚ​ህም ስምዋ ባቢ​ሎን ተባለ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዚያ የም​ድ​ርን ቋንቋ ሁሉ ደባ​ል​ቆ​አ​ልና፤ ከዚ​ያም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ድር ሁሉ ፊት ላይ እነ​ር​ሱን በት​ኖ​አ​ቸ​ዋል።


የሴም ትው​ልድ
( 1ዜ.መ. 1፥24-27 )

10 የሴም ትው​ልድ ይህ ነው። ሴም ከጥ​ፋት ውኃ በኋላ በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመት አር​ፋ​ክ​ስ​ድን በወ​ለደ ጊዜ የመቶ ዓመት ሰው ነበረ።

11 ሴምም አር​ፋ​ክ​ስ​ድን ከወ​ለደ በኋላ አም​ስት መቶ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።

12 አር​ፋ​ክ​ስ​ድም መቶ ሠላሳ አም​ስት ዓመት ኖረ፤ ቃይ​ና​ን​ንም ወለደ፤

13 አር​ፋ​ክ​ስ​ድም ቃይ​ና​ንን ከወ​ለደ በኋላ አራት መቶ አርባ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም። ቃይ​ና​ንም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ሳላ​ንም ወለደ፤ ቃይ​ና​ንም ሳላን ከወ​ለደ በኋላ አራት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ልጆች ወለደ፤ ሞተም።

14 ሳላም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ዔቦ​ር​ንም ወለደ፤

15 ሳላም ዔቦ​ርን ከወ​ለደ በኋላ አራት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።

16 ዔቦ​ርም መቶ ሠላሳ አራት ዓመት ኖረ፤ ፋሌ​ቅ​ንም ወለደ፤

17 ዔቦ​ርም ፋሌ​ቅን ከወ​ለደ በኋላ አራት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።

18 ፋሌ​ቅም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ራግ​ው​ንም ወለደ፤

19 ፋሌ​ቅም ራግ​ውን ከወ​ለደ በኋላ ሁለት መቶ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።

20 ራግ​ውም መቶ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ፤ ሴሮ​ሕ​ንም ወለደ፤

21 ራግ​ውም ሴሮ​ሕን ከወ​ለደ በኋላ ሁለት መቶ ሰባት ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።

22 ሴሮ​ሕም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ናኮ​ር​ንም ወለደ፤

23 ሴሮ​ሕም ናኮ​ርን ከወ​ለደ በኋላ ሁለት መቶ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።

24 ናኮ​ርም መቶ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፤ ታራ​ንም ወለደ፤

25 ታራ​ንም ከወ​ለደ በኋላ ናኮር መቶ ሀያ ዘጠኝ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ፤ ሞተም።


የታራ ትው​ልድ

26 ታራም መቶ ዓመት ኖረ፥ አብ​ራ​ም​ንና ናኮ​ርን፥ አራ​ን​ንም ወለደ።

27 አራ​ንም ሎጥን ወለደ።

28 አራ​ንም በተ​ወ​ለ​ደ​ባት ሀገር በከ​ለ​ዳ​ው​ያን ምድር በአ​ባቱ በታራ ፊት ሞተ።

29 አብ​ራ​ምና ናኮ​ርም ሚስ​ቶ​ችን አገቡ፤ የአ​ብ​ራም ሚስት ስምዋ ሦራ ነው፤ የና​ኮ​ርም ሚስት የአ​ራን ልጅ ሚልካ ናት፤ አራ​ንም የሚ​ል​ካና የዮ​ስካ አባት ነው።

30 ሦራም መካን ነበ​ረች፤ ልጆ​ችም አል​ነ​በ​ሩ​አ​ትም።

31 ታራም ልጁን አብ​ራ​ም​ንና የልጅ ልጁን የአ​ራ​ንን ልጅ ሎጥን፥ የል​ጁ​ንም የአ​ብ​ራ​ምን ሚስት ምራ​ቱን ሦራን ወሰደ፤ ከእ​ር​ሱም ጋር ወደ ከነ​ዓን ምድር ይሄዱ ዘንድ ከከ​ለ​ዳ​ው​ያን ምድር አወ​ጣ​ቸው። ወደ ካራ​ንም መጡ፤ በዚ​ያም ተቀ​መጡ።

32 ታራም በካ​ራን ምድር የኖ​ረ​በት ዘመን ሁለት መቶ አም​ስት ዓመት ሆነ፤ ታራም በካ​ራን ሞተ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos