Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዘዳግም 16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


በዓለ ፋሲካ
( ዘፀ. 12፥1-20 )

1 “በሚ​ያ​ዝያ ወር ከግ​ብፅ ሀገር በሌ​ሊት ወጥ​ተ​ሃ​ልና የሚ​ያ​ዝ​ያን ወር ጠብ​ቀህ፥ የአ​ም​ላ​ክህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፋሲካ አድ​ርግ።

2 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዚያ ስሙ ይጠ​ራ​በት ዘንድ በመ​ረ​ጠው ስፍራ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፋሲካ ከበ​ግና ከላም መንጋ ሠዋ።

3 የቦ​ካ​ውን እን​ጀራ ከእ​ርሱ ጋር አት​ብላ፤ ከግ​ብፅ ሀገር በች​ኮላ ስለ ወጣህ ከግ​ብፅ ሀገር የወ​ጣ​ህ​በ​ትን ቀን በዕ​ድ​ሜህ ሁሉ ታስብ ዘንድ የመ​ከ​ራን እን​ጀራ፥ ቂጣ እን​ጀራ ሰባት ቀን ከእ​ርሱ ጋር ብላ።

4 ሰባት ቀንም በሀ​ገ​ርህ ሁሉ የቦካ አይ​ታ​ይም፤ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ቀን ማታ ከሠ​ዋ​ኸው ሥጋ እስከ ነገ ድረስ ምንም አይ​ደር።

5 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከሰ​ጠህ ከተ​ሞች በማ​ን​ኛ​ዪ​ቱም ፋሲ​ካን ትሠዋ ዘንድ አይ​ገ​ባ​ህም።

6 ነገር ግን አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስሙ ይጠ​ራ​በት ዘንድ በመ​ረ​ጠው በዚያ ስፍራ ከግ​ብፅ በወ​ጣ​ህ​በት ወራት፥ ፀሐይ ሲገባ፥ ማታ ፋሲ​ካን ትሠ​ዋ​ለህ።

7 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በመ​ረ​ጠው ስፍራ ትጠ​ብ​ሰ​ዋ​ለህ፤ ታበ​ስ​ለ​ዋ​ለ​ህም፤ ትበ​ላ​ው​ማ​ለህ፤ በነ​ጋ​ውም ተመ​ል​ሰህ ወደ ቤትህ ትሄ​ዳ​ለህ።

8 ስድ​ስት ቀን ቂጣ እን​ጀራ ብላ፤ ሰባ​ተ​ኛው ቀን ግን መው​ጫው ስለ​ሆነ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዓል ይሁን፤ ለነ​ፍ​ስም ከሚ​ሠ​ራው በቀር ሥራን ሁሉ አታ​ድ​ር​ግ​በት።


የመ​ከር በዓል፤
( ዘፀ. 34፥22 ፤ ዘሌ. 23፥15-21 )

9 “ሰባት ሳም​ን​ትም ትቈ​ጥ​ራ​ለህ፤ መከ​ሩን ማጨድ ከም​ት​ጀ​ም​ር​በት ቀን ጀምሮ ሰባት ሳም​ንት መቍ​ጠር ትጀ​ም​ራ​ለህ።

10 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የባ​ረ​ከ​ህን ያህል እጅህ መስ​ጠት በም​ት​ች​ለው መጠን ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሰ​ባ​ቱን ሱባዔ በዓል ታደ​ር​ጋ​ለህ።

11 አንተ፥ ወንድ ልጅ​ህና ሴት ልጅህ፥ ወንድ ባሪ​ያ​ህና ሴት ባሪ​ያህ፥ በሀ​ገ​ር​ህም ውስጥ ያለው ሌዋዊ፥ በመ​ካ​ከ​ል​ህም ያሉ መጻ​ተ​ኛና ድሃ-አደግ፥ መበ​ለ​ትም አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዚያ ስሙ ይጠ​ራ​በት ዘንድ በሚ​መ​ር​ጠው ስፍራ በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ደስ ይበ​ላ​ችሁ።

12 አን​ተም በግ​ብፅ ባሪያ እንደ ነበ​ርህ ዐስብ፤ ይህ​ንም ሥር​ዐት ጠብቅ፤ አድ​ር​ገ​ውም።


የዳስ በዓል
( ዘሌ. 23፥33-43 )

13 “ከአ​ው​ድ​ማ​ህና ከወ​ይን መጭ​መ​ቂ​ያህ ፍሬ​ህን በሰ​በ​ሰ​ብህ ጊዜ ሰባት ቀን የዳስ በዓል አድ​ርግ።

14 አን​ተም፥ ወንድ ልጅ​ህና ሴት ልጅህ፥ ወንድ ባሪ​ያ​ህና ሴት ባሪ​ያህ፥ በሀ​ገ​ር​ህም ውስጥ ያለ ሌዋ​ዊና መጻ​ተኛ፥ ድሃ-አደ​ግና መበ​ለ​ትም በበ​ዓ​ልህ ደስ ይበ​ላ​ችሁ።

15 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለራሱ በመ​ረ​ጠው ስፍራ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰባት ቀን በዓል ታደ​ር​ጋ​ለህ፤ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በፍ​ሬህ ሁሉ፥ በእ​ጅ​ህም ሥራ ሁሉ ይባ​ር​ክ​ሃ​ልና። አን​ተም ፈጽሞ ደስ ይል​ሃ​ልና።

16 በዓ​መት ሦስት ጊዜ በቂጣ በዓል፥ በሰ​ባቱ ሱባ​ዔም በዓል፥ በዳ​ስም በዓል ወንድ ልጅህ ሁሉ በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በመ​ረ​ጠው ስፍራ ይታይ፤

17 በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ባዶ እጅ​ህን አት​ታይ። አም​ላ​ካ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሰ​ጣ​ችሁ በረ​ከት መጠን እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ችሁ እንደ ችሎ​ታ​ችሁ ታመ​ጣ​ላ​ችሁ።


ስለ ፍርድ አሰ​ጣጥ

18 “አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ሰ​ጥህ በሀ​ገ​ርህ ደጅ ሁሉ በየ​ነ​ገ​ዶ​ችህ ፈራ​ጆ​ች​ንና መባ​ውን የሚ​ጽ​ፉ​ትን ሹሙ፤ ለሕ​ዝ​ቡም ቅን ፍር​ድን ይፍ​ረዱ።

19 ፍር​ድን አታ​ጣ​ምም፤ ፊት አይ​ተ​ህም አታ​ድላ፤ ጉቦን አት​ቀ​በል፥ ጉቦ የጥ​በ​በ​ኞ​ችን ዐይን ያሳ​ው​ራ​ልና፥ የእ​ው​ነ​ት​ንም ቃል ያጣ​ም​ማ​ልና ጉቦ አት​ቀ​በል።

20 በሕ​ይ​ወት ትኖር ዘንድ፥ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ሰ​ጥ​ህን ምድር ትወ​ርስ ዘንድ እው​ነ​ተ​ኛ​ውን ፍርድ ተከ​ተል።


የአ​ም​ልኮ ጣዖት መከ​ላ​ከል

21 “ለአ​ንተ በም​ት​ሠ​ራው በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ አጠ​ገብ ከማ​ና​ቸ​ውም ዛፍ የማ​ም​ለ​ኪያ ዐጸድ አድ​ር​ገህ አት​ት​ከል።

22 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ጠ​ላ​ውን ሐው​ልት ለአ​ንተ አታ​ቁም።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos