Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

ተረፈ ባሮክ 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ተረፈ ባሮክ

1 ኤር​ም​ያ​ስም ጳስ​ኮ​ርን እን​ዲህ አለው፥ “እና​ን​ተስ በዘ​መ​ና​ችሁ ሁሉ ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ሁና ከእ​ና​ንተ በኋላ ከሚ​መጡ ልጆ​ቻ​ችሁ ጋር ጽድ​ቅን ትቃ​ረ​ኗ​ታ​ላ​ችሁ።

2 እነ​ር​ሱስ ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ ይልቅ እጅግ የተ​ና​ቀች ኀጢ​አ​ትን ሠሩ። እነ​ር​ሱም ዋጋ የማ​ይ​ገ​ኝ​ለ​ትን ይሸ​ጡ​ታል፤ ሕማ​ማ​ትን የሚ​ያ​ስ​ወ​ግ​ደ​ውን እን​ዲ​ታ​መም ያደ​ር​ጉ​ታል፤ ኀጢ​አ​ትን የሚ​ያ​ስ​ተ​ሰ​ር​የ​ው​ንም ይፈ​ር​ዱ​በ​ታል።

3 የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የተ​ስ​ማ​ሙ​በ​ትን የክ​ቡ​ሩን ዋጋ ሠላሳ ብር ይቀ​በ​ላሉ፤ ያንም ብር ለሸ​ክላ ሠሪ ቦታ ዋጋ አድ​ር​ገው ይሰ​ጡ​ታል።

4 እዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዳ​ዘ​ዘኝ እን​ዲሁ እና​ገ​ራ​ለሁ።

5 ስለ​ዚህ ንጹሕ ደምን ፈር​ደው አፍ​ስ​ሰ​ዋ​ልና ፍር​ድና ጥፋት በእ​ነ​ርሱ ላይ፥ ከእ​ነ​ር​ሱም በኋላ በል​ጆ​ቻ​ቸው ላይ ይወ​ር​ድ​ባ​ቸ​ዋል፤”

6 ወደ ባቢ​ሎን በተ​ማ​ረኩ ጊዜ ስውር ያል​ሆነ ባሮክ ከተ​ና​ገ​ረው ነገር የቀረ ይህ ነው።

7 እን​ዲ​ህም ሆነ፤ የከ​ለ​ዳ​ው​ያን ንጉሥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች በማ​ረ​ካ​ቸው ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኤር​ም​ያ​ስን ተና​ገ​ረው።

8 እን​ዲ​ህም አለው፥ “ወዳጄ ኤር​ም​ያስ ሆይ፥ ከዚ​ህች ከተማ ውጣ፤ ከሚ​ኖ​ሩ​ባት ሰዎች ኀጢ​አት ብዛት የተ​ነሣ አጠ​ፋ​ታ​ለ​ሁና አን​ተና ባሮክ ውጡ።

9 ልመ​ናህ በከ​ተ​ማ​ዪቱ መካ​ከል እንደ ጽኑ ምሰሶ፥ በዙ​ሪ​ያ​ዋም እንደ አድ​ማስ ቅጥር ነውና፤ አሁ​ንም የከ​ለ​ዳ​ው​ያን ሠራ​ዊት ሳይ​መ​ጣና ሀገ​ሪ​ቱን ሳይ​ከ​ባት ተነ​ሥ​ታ​ችሁ ሂዱ፥ ውጡም።”

10 ኤር​ም​ያ​ስም እን​ዲህ ሲል ተና​ገረ፥ “ጌታዬ ሆይ፥ እለ​ም​ን​ሃ​ለሁ፤ በፊ​ትህ ይና​ገር ዘንድ ባሪ​ያ​ህን እዘ​ዘው።”

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “ወዳጄ ኤር​ም​ያስ ሆይ! ተና​ገር” አለው።

12 ኤር​ም​ያ​ስም እን​ዲህ ሲል ተና​ገረ፥ “ሁሉን የም​ት​ገዛ አቤቱ፥ ንጉሡ ከሠ​ራ​ዊቱ ጋር ይታ​በ​ይና በአ​ም​ላክ ከተማ በረ​ታ​ሁ​ባት ይል ዘንድ የመ​ረ​ጥ​ኻ​ትን ይህ​ቺን ከተማ በከ​ለ​ዳ​ው​ያን እጅ አሳ​ል​ፈህ ትሰ​ጣ​ለ​ህን?

13 አቤቱ፥ ይህ አይ​ሁን፤ ከወ​ደ​ድ​ህም በእ​ጅህ አጥ​ፋት።”

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኤር​ም​ያ​ስን አለው፥ “በሚ​ኖ​ሩ​ባት ሰዎች ኀጢ​አት አጠ​ፋ​ታ​ለ​ሁና አንተ ወዳጄ ስለ ሆንህ ባሮ​ክና አንተ ተነ​ሥ​ታ​ችሁ ውጡ።

15 እኔ አስ​ቀ​ድሜ በሮ​ች​ዋን ካል​ከ​ፈ​ትሁ ንጉ​ሡና ሠራ​ዊቱ ወደ ሀገ​ሪቱ መግ​ባት አይ​ቻ​ላ​ቸ​ውም።

16 አሁ​ንም ተነ​ሥ​ተህ ወደ ባሮክ ሂድ፤ ይህ​ንም ነገር ሁሉ ንገ​ረው፤ ከሌ​ሊቱ ስድ​ስት ሰዓት በሆነ ጊዜ ተነ​ሥ​ታ​ችሁ ወደ ከተ​ማ​ዪቱ ቅጥር ኑ።

17 እኔ አሳ​ያ​ች​ኋ​ለሁ፤ እኔም አስ​ቀ​ድሜ ከተ​ማ​ዪ​ቱን ካላ​ጠ​ፋ​ኋት ወደ እር​ስዋ መግ​ባት አይ​ች​ሉም።”

18 ጌታም ይህን ተና​ግሮ ከኤ​ር​ም​ያስ ዘንድ ሄደ።

19 ያን​ጊ​ዜም ኤር​ም​ያስ ልብ​ሱን ቀደደ፤ በራ​ሱም ላይ ትቢያ ነሰ​ነሰ፤ ወደ ቤተ መቅ​ደ​ስም ገባ።

20 ባሮ​ክም ኤር​ም​ያ​ስን በራሱ ላይ ትቢያ ነስ​ንሶ፥ ልብ​ሶ​ቹ​ንም ቀድዶ ባየው ጊዜ፥ “አባቴ ኤር​ም​ያስ ሆይ፥ ምን ሆንህ? ሕዝ​ቡስ ምን ኀጢ​አት ሠሩ?” ብሎ ቃሉን አሰ​ምቶ ጮኸ።

21 ሕዝቡ በሳቱ ጊዜ ኤር​ም​ያስ ያዝን ነበ​ርና፥ በራ​ሱም ትቢያ ይነ​ሰ​ንስ ነበ​ርና፥ የሕ​ዝ​ቡም በደ​ላ​ቸው እስ​ኪ​ሰ​ረ​ይ​ላ​ቸው ድረስ ለሕ​ዝቡ ይጸ​ል​ይ​ላ​ቸው ነበ​ርና።

22 ባሮ​ክም፥ “አባቴ ኤር​ም​ያስ ሆይ፥ ምን ሆንህ?” ብሎ ጠየ​ቀው። ኤር​ም​ያ​ስም እን​ዲህ አለው፥ “ልቡ​ና​ች​ንን እን​ቅ​ደድ እንጂ ልብ​ሶ​ቻ​ች​ንን እን​ዳ​ን​ቀድ ተጠ​በቅ” አለው።

23 “ከዛሬ ጀምሮ እነ​ዚ​ህን ወገ​ኖች ይቅር አይ​ሏ​ቸ​ው​ምና እን​ባን እስ​ክ​ን​መ​ላ​ቸው ድረስ በሚ​ገባ እና​ለ​ቅስ ዘንድ ወደ ጕድ​ጓ​ዶች ውኃን አን​ጨ​ምር” አለው።

24 ባሮ​ክም፥ “አባቴ ኤር​ም​ያስ ሆይ፥ ምን ሆንህ?” አለ።

25 ኤር​ም​ያ​ስም፥ “አም​ላክ ከተ​ማ​ዋን በከ​ላ​ው​ዴ​ዎን ንጉሥ እጅ አሳ​ልፎ ይሰ​ጣ​ታ​ልና፥ ሕዝ​ቡ​ንም በክፉ ነገር ይማ​ር​ካ​ቸ​ዋ​ልና ነው፤” አለው።

26 ባሮ​ክም ይህን ሁሉ ነገር ሰምቶ ልብ​ሶ​ቹን ቀደ​ደና፥ “አባቴ ኤር​ም​ያስ ሆይ፥ ምን ላኩ​ብህ?” አለው።

27 ኤር​ም​ያ​ስም፥ “ነገ​ሩን በእ​ው​ነት ታውቅ ዘንድ ከሌ​ሊቱ እስከ ስድ​ስት ሰዓት ድረስ ከእኔ ጋር ቈይ” አለው።

28 በቤተ መቅ​ደ​ስም እያ​ለ​ቀሱ ተቀ​መጡ፤ ከሌ​ሊ​ቱም ስድ​ስት ሰዓት በሆነ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኤር​ም​ያ​ስን ይወጣ ዘንድ ነገ​ረው።

29 ከባ​ሮ​ክም ጋር ወጣ፤ ወደ ቅጽ​ሩም ደረሱ፤ እየ​ጸ​ለ​ዩም ተቀ​መጡ።

30 የመ​ለ​ከት ድም​ፅም ተሰማ፤ መላ​እ​ክ​ትም ከሰ​ማ​ያት መጡ፤ በእ​ጃ​ቸ​ውም የእ​ሳት መብ​ራት ይዘው በቅ​ጥሯ ቆመው ነበር።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos