Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ሣልስ 5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የፈ​ጠ​ረ​ህን ዕወ​ቀው፤ ያጸ​ና​ህና ያዳ​ነህ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ቅዱ​ስም አት​ር​ሳው፤ አንተ መሬት ስት​ሆን በመ​ል​ኩና በም​ሳ​ሌው ፈጥ​ሮ​ሃ​ልና ደስ ይልህ ዘንድ፥ ምድ​ር​ንም ትቈ​ፍ​ራት ዘንድ በገ​ነት አኖ​ረህ።

2 ትእ​ዛ​ዙ​ንም ባፈ​ረ​ስህ ጊዜ ከዚያ ከገ​ነት አሜ​ከ​ላና እሾህ ወደ​ም​ታ​በ​ቅል፥ በአ​ን​ተም ምክ​ን​ያት ወደ ረገ​ማት ወደ​ዚች ምድር አወ​ጣህ።

3 አንተ ምድር ነህና፥ እር​ስ​ዋም ምድር ናትና፥ አንተ ትቢያ ነህና፥ እር​ስ​ዋም ትቢያ ናትና፥ አንተ መሬት ነህና እር​ስ​ዋም መሬት ናትና ከእ​ር​ስ​ዋም ትመ​ገ​ባ​ለህ፤ ወደ እር​ስ​ዋም ትመ​ለ​ሳ​ለህ፤ ያስ​ነ​ሣህ ዘንድ እስ​ኪ​ወ​ድድ ድረስ ትቢያ ትሆ​ና​ለ​ህና የሠ​ራ​ኸ​ውን በደ​ልና ኀጢ​አት ሁሉ ይመ​ረ​ም​ር​ሃ​ልና።

4 ያን​ጊዜ የም​ት​መ​ል​ሰ​ውን ዕወቅ፤ በዚ​ህም ዓለም የሠ​ራ​ኸ​ውን ክፉ​ው​ንና በጎ​ውን አስብ፤ ክፉው ይበዛ እንደ ሆነ፥ ወይም በጎው ይበዛ እንደ ሆነ መዝን፤ ምከ​ርም።

5 በጎ ነገ​ር​ንም ብታ​በዛ፥ ሙታን በሚ​ነ​ሡ​በት ቀን ደስ ይል​ህና ሐሤት ታደ​ርግ ዘንድ ለአ​ንተ መል​ካም ይሆ​ን​ል​ሃል።

6 ክፉ ሥራን ብታ​በዛ ግን ወዮ​ልህ፤ እንደ እጅህ ሥራና እንደ ልቡ​ናህ ክፋት ፍዳ​ህን ትቀ​በ​ላ​ለ​ህና በባ​ል​ን​ጀ​ራህ ክፉ እንደ ሠራ​ህ​በት፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም እን​ዳ​ል​ፈ​ራ​ኸው እንደ ሥራህ ፍዳ​ህን ትቀ​በ​ላ​ለ​ህና።

7 ባል​ን​ጀ​ራ​ህ​ንም ብት​ከ​ዳው፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስም በሐ​ሰት ብት​ምል፥ እንደ ሥራህ ፍዳ​ህን ትቀ​በ​ላ​ለ​ህና።

8 ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ በማ​ስ​መ​ሰል ቃል​ህን በሐ​ሰት እው​ነ​ተኛ እን​ዲ​ሆን ታደ​ር​ጋ​ለ​ህና፤ አንተ ግን ሐሰት እንደ ተና​ገ​ርህ ታው​ቀ​ዋ​ለህ።

9 ከአ​ንተ ጋራ ያሉ​ት​ንም እያ​ሳ​መ​ንህ ቃልህ እው​ነት እንደ ሆነ ታጸ​ና​ለህ፤ እው​ነት ያል​ሆነ ነገ​ር​ንም ታበ​ዛ​ለህ፤ እንደ ሥራ​ህም ፍዳ​ህን ትቀ​በ​ላ​ለህ፤ የማ​ት​ሰ​ጠ​ውን ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ እያ​ልህ ባል​ን​ጀ​ራ​ህን ትከ​ዳ​ዋ​ለህ።

10 በን​ጹሕ ልቡ​ና​ህም እሰ​ጣ​ለሁ ባልህ ጊዜ አጋ​ን​ንት እንደ ውሾች ደጅ ይጠ​ኑ​ሃል፤ ሁሉ​ንም ያስ​ረ​ሱ​ሃል፤ ብት​ነ​ሣም፥ ትሰጥ ዘንድ ብት​ወ​ድም የማ​ይ​ጠ​ቅ​ም​ህ​ንና የማ​ት​በ​ላ​ውን ገን​ዘብ ታደ​ልብ ዘንድ የዚህ ዓለም ገን​ዘብ ያስ​ጎ​መ​ጅ​ሃል፤ “ይሰ​በ​ስ​ባሉ፤ የሚ​ሰ​በ​ስ​ቡ​ለ​ት​ንም አያ​ው​ቁም” ብሏ​ልና።

11 ዳግ​መ​ኛም “ሐሰ​ተ​ኞች የአ​ዳም ልጆች ሚዛ​ንን ሐሰ​ተኛ ያደ​ር​ጋሉ፤ እነ​ር​ሱስ መቼም መች ከከ​ንቱ ወደ ከንቱ ይሄ​ዳሉ” ብሏ​ልና።

12 ሰዎች ሆይ ሚዛ​ን​ንና ላዳ​ንን በማ​ሳ​በል፥ የሌ​ላ​ው​ንም ገን​ዘብ በመ​ስ​ረ​ቅና በዐ​መፅ ወደ ገን​ዘ​ባ​ችሁ በመ​ጨ​መር፥ የባ​ል​ን​ጀ​ራ​ች​ሁ​ንም ገን​ዘብ፥ የባ​ል​ን​ጀ​ራ​ች​ሁ​ንም እርሻ በመ​ድ​ፈር፥ ለባ​ል​ን​ጀ​ራ​ችሁ ያይ​ደለ ለራ​ሳ​ችሁ ትርፍ በም​ታ​ደ​ር​ጉት ሁሉ ዐመ​ፅን ተስፋ አታ​ድ​ር​ጓት።

13 ይህ​ንም ብታ​ደ​ርጉ እንደ ሥራ​ችሁ ትቀ​በ​ላ​ላ​ችሁ።

14 ሰዎች ሆይ በሚ​ገባ በእ​ጃ​ችሁ ሥራ ተመ​ገቡ እንጂ ቅሚ​ያን አት​ታ​መ​ኗት፤ በማ​ይ​ገባ ያለ ፍርድ በመ​ቀ​ማ​ትና በመ​ን​ጠቅ የሰ​ውን ገን​ዘብ ትበሉ ዘንድ አት​ው​ደዱ።

15 ብት​በ​ሉ​ትም አያ​ጠ​ግ​ባ​ች​ሁም፤ ብታ​ደ​ል​ቡ​ትም በም​ት​ሞ​ቱ​በት ጊዜ ለሌላ ትተ​ዉ​ታ​ላ​ችሁ እንጂ አይ​ጠ​ቅ​ማ​ች​ሁም።

16 ገን​ዘ​ባ​ች​ሁም ቢበዛ ልቡ​ና​ች​ሁን አታ​ኵሩ፤ የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ሰዎች ገን​ዘብ ከም​ድጃ እን​ደ​ሚ​ወጣ፥ ነፋ​ስም እን​ደ​ሚ​ወ​ስ​ደው እንደ ጢስ ነውና፥ ከብዙ የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ገን​ዘብ በእ​ው​ነት ያለ ጥቂት ገን​ዘብ ይሻ​ላል።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos