Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ካልእ 9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ዕዝ​ራም ከቤተ መቅ​ደሱ አደ​ባ​ባይ ተነ​ሥቶ ወደ ናሴሩ ልጅ ወደ ዮሐ​ናን ቤት ሄደ።

2 በዚ​ያም ተቀ​ምጦ ስለ ታላ​ላ​ቆ​ችና ብዙ​ዎች ኀጢ​አ​ቶ​ቻ​ቸው እያ​ለ​ቀሰ እህ​ልን አል​በ​ላም፤ ውኃ​ንም አል​ጠ​ጣም።

3 ከዚህ በኋላ ከም​ርኮ ለተ​መ​ለሱ ሁሉ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ይገኙ ዘንድ፥

4 እስከ ሁለ​ትና እስከ ሦስት ቀን ድረስ ያል​ተ​ገ​ኙና ያል​ደ​ረሱ ሁሉ እንደ ሥር​ዐ​ታ​ቸው በአ​ለ​ቆ​ቻ​ቸው ቅጣት ይቀጡ ዘንድ፥ ከብ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ይወ​ረሱ ዘንድ፥ እነ​ር​ሱም ከወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው ይለዩ ዘንድ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ዐዋጅ ነገ​ረ​ላ​ቸው።

5 የይ​ሁ​ዳና የብ​ን​ያም ወገ​ኖ​ችም በዘ​ጠ​ነ​ኛው ወር በሃ​ያ​ኛው ቀን በሦ​ስት ቀን ውስጥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ተሰ​በ​ሰቡ።

6 ሁሉም በቤተ መቅ​ደሱ አደ​ባ​ባይ ተቀ​መጡ፤ ክረ​ምት ነበ​ርና ስለ ውርጩ ጽናት ይን​ቀ​ጠ​ቀጡ ነበር።

7 ዕዝ​ራም ተነ​ሥቶ እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “ከአ​ሕ​ዛብ ወገን ሚስት ያገ​ባ​ችሁ እና​ንተ በደ​ላ​ችሁ፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ላይ ኀጢ​አ​ትን ጨመ​ራ​ችሁ።

8 አሁ​ንም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተና​ዘዙ፤ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ን​ንም አም​ላክ አመ​ስ​ግ​ኑት።

9 ፈቃ​ዱ​ንም ፈጽሙ፤ ከም​ድር አሕ​ዛ​ብና ከባ​ዕ​ዳት ሚስ​ቶ​ቻ​ች​ሁም ተለዩ።”

10 ሁሉም በሙሉ በታ​ላቅ ድምፅ ጮኸው እን​ዲህ አሉት፥ “እሺ አንተ እን​ዳ​ዘ​ዝ​ኸን እና​ደ​ር​ጋ​ለን።

11 ነገር ግን ሰዉ ብዙ ነው፤ ጊዜ​ውም ክረ​ምት ነው፤ ፈጥ​ነ​ንም እና​ደ​ር​ገው ዘንድ አን​ች​ልም፤ ሥራ​ውም የአ​ንድ ቀን ወይም የሁ​ለት ቀን ሥራ አይ​ደ​ለም፤ በዚህ ፈጽ​መን በድ​ለ​ና​ልና።

12 አሁ​ንም ከልዩ ወገን ሚስት ያገቡ መሳ​ፍ​ንት ሁሉና መን​ደ​ረ​ተ​ኞ​ችም ተሰ​ብ​ስ​በው ይምጡ።

13 በዚህ ሥራ ያገ​ኘን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍጣ ከእኛ ይርቅ ዘንድ መን​ደ​ረ​ተ​ኞ​ቻ​ቸ​ው​ንና ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ቻ​ቸ​ውን፥ አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ይቅ​ጠ​ሯ​ቸው።”

14 የአ​ዛ​ሄል ልጅ ዮና​ታን፥ የታ​ቃኑ ልጅ ኢያ​ዝ​ያ​ስም መጡ፤ ሞሶ​ላ​ሞስ፥ ሌዊ፥ ሳባ​ጢ​ዎስ፥ እነ​ር​ሱም እን​ዲህ ተባ​በሩ።

15 ከም​ርኮ የተ​መ​ለ​ሱ​ትም ሁሉ እን​ዲሁ አደ​ረጉ።

16 ካህኑ ዕዝ​ራም ካገ​ሮ​ቻ​ቸው ሽማ​ግ​ሌ​ዎች፥ በያ​ገ​ራ​ቸ​ውም ከሚ​ኖ​ሩት ሁሉ ስማ​ቸው ልዩ ልዩ የሆነ ሰዎ​ችን መረጠ፤ እን​ዲ​ህም ያደ​ርጉ ዘንድ እስከ ዐሥ​ረ​ኛው ወር መባቻ ድረስ ተቃ​ጠሩ።

17 ከልዩ ወገን ሚስት ያገቡ እነ​ዚ​ያም ሰዎች ሁሉ “እስከ መጀ​መ​ሪ​ያው ወር መባቻ እን​ፈ​ታ​ለን” ብለው ነገ​ራ​ቸ​ውን ጨረሱ።

18 ከካ​ህ​ና​ቱም ውስጥ ከባ​ዕድ ወገን ሚስት ያገቡ ተገኙ።

19 እነ​ር​ሱም የኢ​ዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ የኢ​ያሱ ልጆ​ችና ወን​ድ​ሞቹ፥ ማቴ​ላስ፥ አል​ዓ​ዛር፥ ዮሬ​ቦ​ስና ዮአ​ዳ​ኖ​ስም ናቸው።

20 ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ፈት​ተው ስለ ኀጢ​አ​ታ​ቸው መሥ​ዋ​ዕት ይሠዉ ዘንድ ጀመሩ።

21 ከኤ​ሞ​ርም ልጆች ሐና​ንያ፥ ዘብ​ዴ​ዎስ፥ ሜኑስ፥ ሴሜ​ዎስ፥ ኢያ​ር​ማ​የ​ልና አዛ​ርያ ናቸው።

22 ከፌ​ት​ር​ኤ​ልም ልጆች ኢል​ዮ​ኒስ፥ ማስ​ያስ፥ አስ​ማ​ኤ​ሎስ፥ ናት​ና​አ​ሎስ፥ ዎቅ​ዲ​ሎ​ስና አል​ታሳ ናቸው።

23 ከሌ​ዋ​ው​ያ​ንም ወገን ዮዛ​ባ​ዶስ፥ ሳም​ያስ፥ ቃሊ​ጣስ የሚ​ሉት ቆዮስ፥ ፋት​ያስ፥ ይሁ​ዳና ዮናስ ናቸው።

24 ከመ​ዘ​ም​ራ​ንም ወገን ኤል​ያ​ሳ​ቦ​ስና ባካ​ሮስ ናቸው።

25 ከበ​ረ​ኞ​ችም ወገን ሴሎ​ምና ጦል​ባ​ኒስ ናቸው።

26 ከእ​ስ​ራ​ኤል ከፎ​ሮስ ልጆች ወገ​ንም ኢየ​ር​ማስ፥ ኤዝ​ያስ፥ ሚል​ክ​ያስ፥ ሚያ​ኤ​ሎስ፥ አል​ዓ​ዛር፥ አስ​ብ​ያስ፥ ባኒ​ያስ ናቸው።

27 ከኤላ ልጆች ወገን ማጣ​ን​ያስ፥ ዘካ​ር​ያስ፥ ኢያ​ዚ​ሬ​ሎስ፥ አብ​ድ​ዮስ፥ ኢያ​ሬ​ሞ​ትና ኤዲ​ያስ ናቸው።

28 ከዛ​ሞ​ትም ልጆች ወገን ኤሊ​ያ​ዳስ፥ ኤሊ​ያ​ሲ​ሞስ፥ ኦቶ​ን​ያስ፥ ኢያ​ሪ​ሞስ፥ ሳባ​ቶስ፥ ዘራ​ሊ​ያስ ናቸው።

29 ከቤ​ባ​ይም ልጆች ወገን ዮሐ​ንስ፥ ሐና​ንያ፥ ዮዛ​ብ​ዴ​ዎስ፥ አሜ​ቴ​ዎስ ናቸው።

30 ከማኒ ልጆ​ችም ወገን ኦላ​ሞስ፥ ማም​ኮስ፥ ኢያ​ዴ​ዎስ፥ ኢያ​ሶ​ቦስ፥ አስ​ሔ​ሎስ፥ ኢያ​ር​ሞት ናቸው።

31 ከዓዲ ልጆ​ችም ናሐ​ቶስ፥ ሞሐ​ስ​ያስ፥ ለቁ​ናስ፥ ኒዶስ፥ ቢስ​ቀስ-ጰስ​ሚስ ሲአ​ቱል ባል​ኑስ፥ ሜና​ስ​ያስ ናቸው፥

32 ከሐ​ና​ንያ ልጆ​ችም ኢሊ​ዮ​ሳስ፥ አስ​ያስ፥ ሚል​ክ​ያስ፥ ስብ​ያስ፥ ስም​ዖን፥ ኮሳ​ሜ​ዎስ ናቸው።

33 ከአ​ሶም ልጆ​ችም መል​ጠ​ኒ​ዎስ፥ መጣ​ቲ​ያስ፥ ሳባ​ኔ​ዎስ፥ ኤሌ​ፍ​ላት፥ ምናሴ፥ ሴሜይ ናቸው።

34 ከባኒ ልጆ​ችም ኤር​ም​ያስ፥ ሞም​ዲስ፥ ስማ​ኤል፥ ኢዮ​ኤል፥ መምዲ፥ ጴዴ​ያስ፥ አናስ፥ ቀሪ​ባ​ሶን፥ አና​ሲ​ቦስ፥ መን​ጠ​ኒ​ሞስ፥ አል​ያ​ሲስ፥ በኑስ፥ ኤል​ያሊ፥ ሰማ​ይስ፥ ሰላ​ም​ያስ፥ ናታ​ን​ያስ ናቸው። ከኤ​ዛ​ር​ያስ ልጆ​ችም ሴሲስ፥ ኤዝ​ርል፥ አዛ​ኤል፥ ሳማ​ጢስ፥ ዘም​በሪ፥ ኢዮ​ሶ​ፎስ ናቸው።

35 ከነ​ሐማ ልጆ​ችም ማዚ​ጢ​ያስ፥ ዘቢ​ዲ​ያስ፥ ኤዴስ፥ ኢዮ​ኤል፥ በኒ​ያስ ናቸው።

36 ከባ​ዕ​ዳን ከአ​ሕ​ዛብ ወገን ሚስት ያገ​ቡት ሰዎች ሁሉ ሚስ​ቶ​ቻ​ች​ውን ሁሉ ከል​ጆ​ቻ​ቸው ጋር አስ​ወ​ጧ​ቸው።

37 ካህ​ና​ትና ሌዋ​ው​ያ​ንም፥ ብዙ​ዎች እስ​ራ​ኤ​ልም በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር መባቻ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም በያ​ገ​ራ​ቸው ተቀ​መጡ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች በየ​አ​ው​ራ​ጃ​ቸው ተመ​ለሱ።

38 በቤተ መቅ​ደሱ በር በም​ሥ​ራ​ቃ​ዊው አደ​ባ​ባይ ሁሉም በአ​ን​ድ​ነት ተሰ​በ​ሰቡ።

39 ካህ​ኑ​ንና ጸሓ​ፊ​ዉን ዕዝ​ራ​ንም የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሰ​ጠ​ውን የሙ​ሴን ሕግ ያመጣ ዘንድ ነገ​ሩት።

40 የካ​ህ​ናት አለቃ ዕዝ​ራም በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር መባቻ ለሕ​ዝቡ፥ ለወ​ን​ዶ​ችም፥ ለሴ​ቶ​ችም ለካ​ህ​ና​ቱም ሁሉ ሕጉን ይሰሙ ዘንድ አነ​በ​በ​ላ​ቸው።

41 በቤተ መቅ​ደ​ሱም በር ባለው አደ​ባ​ባይ በወ​ን​ዶ​ቹና በሴ​ቶቹ ፊት ከነ​ግህ ጀምሮ እስከ ቀትር ድረስ አነ​በ​በ​ላ​ቸው፤ ሁሉም በፍ​ጹም ልባ​ቸው ሕጉን አደ​መጡ።

42 ካህ​ኑና የሕጉ ጸሓፊ ዕዝ​ራም ከእ​ን​ጨት በተ​ሠራ መረ​ባ​ርብ ላይ ቆመ።

43 ከእ​ር​ሱም ጋር፦ መተ​ጢ​ያ​ስን፥ ሳሙ​ስን፥ ሐና​ን​ያን፥ አዛ​ር​ያን፥ ኡር​ያ​ስን፥ ሕዝ​ቅ​ያ​ስን፥ በአ​ል​ስ​ሞ​ስ​ንም በቀኙ አቆ​ማ​ቸው።

44 በግ​ራ​ውም በኩል ፈሐ​ል​ዴ​ዎ​ስን፥ ሚሳ​ኤ​ልን፥ ሚል​ክ​ያ​ስን፥ ሎታ​ሳ​ብ​ስን፥ ናባ​ሪ​ያ​ንና ዘካ​ር​ያ​ስን አቆመ።

45 ዕዝ​ራም ያን መጽ​ሐፍ ይዞ በሕ​ዝቡ ፊት ተቀ​መጠ፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ ያከ​ብ​ሩት ነበር።

46 የሕ​ጉ​ንም መጽ​ሐፍ በገ​ለጠ ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ ተነ​ሥ​ተው ቆሙ፤ አዛ​ር​ያም ሁሉን የሚ​ገዛ ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ገ​ነው።

47 ሁሉም በሙሉ፥ “አሜን፥ አሜን” ብለው መለ​ሱ​ለት፤ እጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ወደ ላይ አን​ሥ​ተው በም​ድር ወድ​ቀው ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰገዱ።

48 ሌዋ​ው​ያ​ኑም ኢያሱ፥ አኑሲ፥ ሰራ​ቢ​ያስ፥ ኢያ​ዲ​ኖስ፥ ኢያ​ቆ​ብስ፥ ሳብ​ጣ​ያስ፥ አው​ጥ​ያስ፥ ሚሐና፥ ቀሊ​ጦስ፥ አዛ​ርያ፥ ጠዛ​ብ​ዶስ፥ ሐኒ​ያስ፥ ፈል​ጣስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ አስ​ተ​ማ​ሯ​ቸው።

49 ባነ​በ​በ​ላ​ቸ​ውም ጊዜ ሁሉም በአ​ን​ድ​ነት ሆነው ሰሙ።

50 አጠ​ራ​ጢም የካ​ህ​ና​ቱን አለ​ቃና ጸሓ​ፊ​ውን ዕዝ​ራን፥ ለሁሉ የሚ​ያ​ስ​ተ​ምሩ ሌዋ​ው​ያ​ን​ንም እን​ዲህ አላ​ቸው፦

51 “ይቺ ቀን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ቀ​ደ​ሰች ናት፥” ሁሉም ሕጉን በሰሙ ጊዜ አለ​ቀሱ።

52 እን​ዲ​ህም ተባ​ባሉ፥ “ሂዱና ምሳ​ች​ሁን ብሉ፤ ጠጡም፤ ለሌ​ላ​ቸ​ውም ሰዎች ምጽ​ዋ​ትን ላኩ። ይቺ ቀን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ቀ​ደ​ሰች ናትና፥ አት​ዘ​ኑም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አይ​ጥ​ላ​ች​ሁ​ምና።”

53 ሌዋ​ው​ያ​ንም ሕዝ​ቡን ሁሉ እን​ዲህ ብለው አዘዙ “ይቺ ቀን የተ​ቀ​ደ​ሰች ናትና አት​ዘኑ።”

54 ሁሉም ሊበ​ሉና ሊጠጡ፥ ደስ​ታም ሊያ​ደ​ርጉ፥ ለሌ​ላ​ቸ​ውም ሰዎች ምጽ​ዋ​ትን ሊሰጡ ሄዱ።

55 በተ​ሰ​በ​ሰ​ቡ​በት ቦታም ያስ​ተ​ማ​ሯ​ቸ​ውን ቃል በሰሙ ጊዜ ታላቅ ደስ​ታን አደ​ረጉ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos