Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ካልእ 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ዕዝራ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም እንደ መጣ

1 ከዚ​ህም በኋላ በፋ​ርስ ንጉሥ በአ​ር​ጤ​ክ​ስስ መን​ግ​ሥት ዕዝራ መጣ፤ እር​ሱም የሠ​ራያ ልጅ፥ የአ​ዛ​ር​ያስ ልጅ፥ የኬ​ል​ቅዩ ልጅ፥ የሴ​ሎም ልጅ፤

2 የሳ​ዶቅ ልጅ፥ የአ​ኪ​ጦብ ልጅ፥ የአ​ማ​ር​ትዩ ልጅ፥ የአ​ዝ​ያን ልጅ፥ የቡቂ ልጅ፥ የአ​ቢሱ ልጅ፥ የፊ​ን​ሐስ ልጅ፥ የአ​ል​ዓ​ዛር ልጅ፥ የመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ካህን የአ​ሮን ልጅ፤

3 ይህም ዕዝራ ከባ​ቢ​ሎን መጣ፤ እር​ሱም የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ የሰ​ጠ​ውን የሙ​ሴን ኦሪት ሁሉ ያውቅ ነበረ፤ እር​ሱም ጸሓፊ ነበር።

4 ንጉ​ሡም ክብ​ርን ሰጠው፤ በፊቱ ባለ​ሟ​ል​ነ​ትን አግ​ኝ​ት​ዋ​ልና፥ በሁ​ሉም ላይ ሹሞ​ታ​ልና።

5 ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች፥ ከካ​ህ​ና​ቱና ከሌ​ዋ​ው​ያኑ፥ ከመ​ዘ​ም​ራ​ኑና ከበ​ረ​ኞች፥ ከቤተ መቅ​ደስ አገ​ል​ጋ​ዮ​ችም፥ ዐያ​ሌ​ዎቹ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ወጡ።

6 በአ​ር​ጤ​ክ​ስስ በሰ​ባ​ተ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥቱ፥ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ወር፥ በወሩ መባቻ ከባ​ቢ​ሎን ወጡ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መን​ገ​ዳ​ቸ​ውን እን​ዳ​ቀ​ና​ላ​ቸው በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር መባቻ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ደረሱ።

7 ዕዝ​ራም ብዙ ትም​ህ​ርት የሚ​ያ​ውቅ ነበረ፤ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሥር​ዐ​ት​ንና ፍር​ድን ያስ​ተ​ምር ዘንድ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግና ትእ​ዛዝ የሚ​ጐ​ድ​ለው አል​ነ​በ​ረም።


ንጉሥ አር​ጤ​ክ​ስስ ለዕ​ዝራ የሚ​ፈ​ል​ገው ሁሉ እን​ዲ​ደ​ረ​ግ​ለት የሰ​ጠው ትእ​ዛዝ

8 ንጉሡ አር​ጤ​ክ​ስ​ስም ወደ ካህ​ኑና የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ ወደ​ሚ​ጽ​ፈው ወደ ዕዝራ ደብ​ዳቤ ላከ። ከአ​ር​ጤ​ክ​ስ​ስም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ ወደ​ሚ​ጽ​ፈው ወደ ካህኑ ዕዝራ የተ​ላ​ከው ደብ​ዳቤ እን​ዲህ ይላል፦

9 “ከን​ጉሠ ነገ​ሥት ከአ​ር​ጤ​ክ​ስስ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ጸሓፊ፥ ለካ​ህኑ ለዕ​ዝራ ሰላም ለአ​ንተ ይሁን፤

10 እኔ ሰውን በመ​ው​ደድ አስቤ ከአ​ይ​ሁድ ወገን በመ​ን​ግ​ሥቴ ካሉ ከካ​ህ​ና​ትና ከሌ​ዋ​ው​ያን ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ይሄዱ ዘንድ የሚ​ወ​ዱ​ትን ሁሉ ከአ​ንተ ጋር ይሂዱ ብዬ አዝ​ዣ​ለሁ።

11 ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ይሄዱ ዘንድ የሚ​ወዱ ሁሉ ይሁ​ዳ​ንና ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን አይ​ተው ከእ​ና​ንተ ጋር ይተ​ባ​በሩ።

12 እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ሄደው ያደ​ርጉ ዘንድ እኔና ሰባቱ ባለ​ሟ​ሎች፥ አማ​ካ​ሪ​ዎ​ችም እን​ዲህ አዝ​ዘ​ናል።

13 እኔና ባለ​ሟ​ሎች የተ​ሳ​ል​ነ​ውን ቍር​ባን፥ በባ​ቢ​ሎን ሀገር የተ​ገ​ኘ​ው​ንም ወር​ቁ​ንና ብሩን ሁሉ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያቀ​ርቡ ዘንድ፥

14 ሕዝቡ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ ከሚ​ያ​ገ​ቡት ስእ​ለት ጋራ ወር​ቁ​ንና ብሩን፥ ለበ​ሬ​ዎች፥ ለፍ​የ​ሎ​ችና ለበ​ጎች መግዣ ይሰ​ብ​ስቡ፥

15 እንደ ሥር​ዐ​ታ​ቸው በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ መሥ​ዋ​ዕት ይሠዉ ዘንድ፥

16 ለሚ​ያ​ስ​ፈ​ል​ጋ​ቸው ሁሉ፥ ከባ​ል​ን​ጀ​ራህ ጋር ታደ​ር​ገው ዘንድ የም​ት​ወ​ደ​ውን ሁሉ በዚህ ወር​ቅና ብር እንደ አም​ላ​ክህ ፈቃድ አድ​ርግ።

17 በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ላለ ለአ​ም​ላ​ክህ ቤተ መቅ​ደስ ግዳጅ የሚ​ሆ​ነ​ውን ንዋ​ያተ ቅድ​ሳት።

18 ለአ​ም​ላ​ክህ ቤተ መቅ​ደስ ግዳጅ የም​ት​ሻው ሌላም ቢኖር ከን​ጉሡ ዕቃ ቤት እሰ​ጣ​ለሁ።

19 “እኔ ንጉሥ አር​ጤ​ክ​ስስ የል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ የሚ​ጽፍ ካህኑ ዕዝራ የሚ​ጠ​ይ​ቀ​ውን ሁሉ በሶ​ር​ያና በፊ​ን​ቂስ ካለው ዕቃ ቤት እን​ዲ​ሰ​ጡት አዘ​ዝሁ። ስጡ፤ እን​ቢም አት​በሉ።

20 እስከ መቶ መክ​ሊት ብር፥ ዳግ​መ​ኛም እስከ መቶ የቆ​ሮስ መስ​ፈ​ሪያ ስንዴ፥ እስከ መቶም የኔ​ባል መስ​ፈ​ሪያ ወይን፥ ብዙ ጨውም ቢሆን ስጡ።

21 በን​ጉሥ መን​ግ​ሥ​ትና በል​ጆቹ ላይ መከራ እን​ዳ​ይ​መጣ በል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ይሥሩ።

22 ከካ​ህ​ና​ቱና ከሌ​ዋ​ው​ያኑ፥ ከመ​ዘ​ም​ራ​ኑና ከበ​ረ​ኞቹ ግብር አት​ቀ​በሉ። ከቤተ መቅ​ደ​ስም አገ​ል​ጋ​ዮች፥ ተቀ​ጥ​ረው ቤተ መቅ​ደ​ስን ከሚ​ያ​ገ​ለ​ግሉ ሁሉ ምንም አት​ቀ​በሉ፥ አት​ግ​ዟ​ቸ​ውም።

23 “አን​ተም ዕዝራ! እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በገ​ለ​ጠ​ልህ ጥበብ የአ​ም​ላ​ክን ሕግ ከሚ​ያ​ውቁ ወገ​ኖች ውስጥ ሶር​ያ​ንና ፊን​ቂ​ስን የሚ​ገዙ መኳ​ን​ን​ቱ​ንና መሳ​ፍ​ን​ቱን ሹም፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ የማ​ያ​ው​ቁ​ት​ንም አስ​ተ​ም​ራ​ቸው።

24 የአ​ም​ላ​ክ​ህን ሕግና የን​ጉ​ሡን ትእ​ዛዝ የሚ​ተ​ላ​ለ​ፈ​ው​ንም ሁሉ ቸል አት​በሉ፤ ቅጡ፤ በሞ​ትም ቢሆን፥ በግ​ር​ፋ​ትም ቢሆን፥ በባ​ር​ነ​ትም ቢሆን፥ በመ​ው​ረ​ስም ቢሆን፥ ሁሉ​ንም በየ​ኀ​ጢ​አቱ ቅጡት።”


ዕዝራ አም​ላ​ኩን እን​ዳ​መ​ሰ​ገነ

25 ዕዝ​ራም እን​ዲህ አለ፥ “በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያለ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ያከ​ብር ዘንድ ይህን ነገር በን​ጉሥ ልብ ያሳ​ደረ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይመ​ስ​ገን።

26 በነ​ገ​ሥ​ታ​ቱና በአ​ማ​ካ​ሪ​ዎቹ፥ በወ​ዳ​ጆ​ቹና በመ​ኳ​ን​ንቱ ሁሉ ፊት እኔን አክ​ብ​ሮ​ኛ​ልና።

27 ከዚ​ህም በኋላ በፈ​ጣ​ሪዬ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸጋ ታመ​ንሁ። ከእ​ኔም ጋር ይወጡ ዘንድ ከእ​ስ​ራ​ኤል ሰዎ​ችን ወሰ​ድሁ።”


ከም​ርኮ የተ​መ​ለሱ

28 በን​ጉሡ በአ​ር​ጤ​ክ​ስስ መን​ግ​ሥት በየ​ሀ​ገ​ራ​ቸ​ውና በየ​አ​ው​ራ​ጃ​ቸው ግዛት ከእኔ ጋር ከባ​ቢ​ሎን የወጡ አለ​ቆ​ችም እነ​ዚህ ናቸው።

29 ከፎ​ሮስ ልጆች ጣስ​ጣ​ሞስ፥ ከኢ​ዮ​ጥ​ማ​ሩም ልጆች ጋሜ​ሎስ፥ ከዳ​ዊ​ትም ልጆች የሴ​ኬ​ን​ያስ ልጅ አጡስ፥

30 ከፋ​ሬ​ስም ልጆች ዘካ​ር​ያስ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር መቶ አምሳ ሰዎች ተቈ​ጠሩ።

31 ከፎ​አት ሞዓ​ብም ልጆች የዛ​ርያ ልጅ ኤሊ​ዎ​ንያ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ሁለት መቶ ሰዎች።

32 ከዘ​ቶ​ይ​ስም ልጆች የኢ​ያ​ሐ​ቲሉ ልጅ ኢያ​ኬ​ን​ያስ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ሁለት መቶ ሰዎች፥ ከአ​ዲኑ ልጆች የዮ​ና​ታን ልጅ ኦቤድ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ሁለት መቶ አምሳ ሰዎች።

33 ከኤ​ላም ልጆች የጎ​ቶ​ልያ ልጅ ኢሴይ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ሰባ ሰዎች።

34 ከሳ​ፋጢ ልጆች የሚ​ካ​ኤል ልጅ ዛር​ያስ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ሰባ ሰዎች።

35 ከኢ​ዮ​አ​ብም ልጆች የኢ​ዝ​ኤል ልጅ ኦባ​ድያ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ሁለት መቶ ዐሥራ ሁለት ሰዎች።

36 ከባኒ ልጆ​ችም የኢ​ዮ​ሳ​ፌይ ልጅ አስ​ሊ​ሞት፥ ከእ​ር​ሱም ጋር መቶ ስድሳ ሰዎች።

37 ከቤ​ዔር ልጆ​ችም የባቢ ልጅ ዘካ​ር​ያስ፥ ከር​ሱም ጋር ሃያ ስም​ንት ሰዎች።

38 ከአ​ሰ​ጣ​ያ​ትም ልጆች የአ​ዝ​ጋድ ልጅ ዮሐ​ንስ፥ ከር​ሱም ጋር መቶ ዐሥር ሰዎች።

39 ከአ​ዶ​ኒ​ቃም ልጆች የቀ​ሩት ሁሉ ስማ​ቸው ይህ ነው፦ ኤሊ​ፋሊ፥ ይዑ​ኤል፥ ሰሚ​ያስ፥ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋራ ሰባ ሰዎች።

40 ከቤ​ኑ​ስም ልጆች የአ​ስ​ጣ​ስ​ቆሩ ልጅ ዑታይ ከእ​ር​ሱም ጋራ ሰባ ሰዎች ተቈ​ጠሩ።


ዕዝራ የቤተ መቅ​ደስ ካህ​ና​ትና ሌዋ​ው​ያ​ንን እን​ዳ​ገኘ

41 ቴራን ወደ​ሚ​ባል ወን​ዝም ሰበ​ሰ​ብ​ኋ​ቸው፤ በዚ​ያም ሦስት ቀን አደ​ርን፤ አስ​ቈ​ጠ​ር​ኋ​ቸ​ውም።

42 ከው​ስ​ጣ​ቸ​ውም ካህ​ና​ት​ንና ሌዋ​ው​ያ​ንን አላ​ገ​ኘ​ንም።

43 ወደ አል​ዓ​ዛ​ርም ላክሁ፤ ከእ​ኔም ጋር መአ​ስ​መ​ንን፥ አን​ዐ​ጣ​ንን፥ ሰም​ያ​ስን፥ ኢዮ​ሪ​ቦን፥ ናታ​ንን፥ አር​ጦ​ንን፥ ዘካ​ር​ያ​ስን፥ ሞሱ​ላ​ሞ​ስን ወሰ​ድሁ።

44 ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር ከመ​ሳ​ፍ​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ከዐ​ዋ​ቂ​ዎ​ቻ​ቸው ወሰ​ድሁ።

45 ወደ ዕቃ ቤቱም ሹም ወደ ያድ​ዮን ይሄዱ ዘንድ ነገ​ር​ኋ​ቸው።

46 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ካህ​ና​ትን እን​ዲ​ል​ኩ​ልን ለያ​ድ​ዮ​ንና ለወ​ን​ድ​ሞቹ፥ በዚ​ያም ቦታ ለአሉ ሰዎች ይነ​ግ​ሯ​ቸው ዘንድ አዘ​ዝ​ኋ​ቸው።

47 ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጅ ከሌዊ ልጅ ከሞ​ሐሊ ልጆች ጠቢ​ባን ሰዎ​ችን አሲ​ብ​ያ​ንና ልጆ​ቹን፥ ዐሥራ ስም​ንት ወን​ድ​ሞ​ቹ​ንም አመ​ጡ​ልን፥

48 ከከ​ዓኑ ልጆ​ችና ከል​ጆ​ቻ​ቸ​ውም ውስጥ የሆኑ ሃያ ሰዎች፥

49 ዳዊት የሠ​ራ​ቸው የቤተ መቅ​ደስ አገ​ል​ጋ​ዮ​ችና አለ​ቆ​ቻ​ቸው ለሌ​ዋ​ው​ያን ሥራ የተ​ጨ​መሩ የካ​ህ​ናት ልጆች ሁለት መቶ ሃያ ናቸው፤ የሁ​ሉም ስማ​ቸው ተጻፈ።


ዕዝራ ጾምን እን​ዳ​ወጀ

50 በአ​ም​ላ​ካ​ችን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ከል​ጆ​ቻ​ችን ጋራ በዚያ እን​ጾም ዘንድ ለል​ጆ​ቻ​ች​ንና ለከ​ብ​ቶ​ቻ​ች​ንም ይቅ​ር​ታን እን​ለ​ምን ዘንድ ተሳ​ልን።

51 ሀገ​ራ​ች​ንን የሚ​ያ​ጸ​ኑና ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችን ጋራ የሚ​መ​ካ​ከቱ እግ​ረ​ኞ​ች​ንና ፈረ​ሰ​ኞ​ችን እን​ዲ​ሰ​ጠን ለን​ጉሡ እልክ ዘንድ አፍ​ሬ​አ​ለ​ሁና።

52 ሥራ​ውን ሁሉ ያቀ​ና​ላ​ቸው ዘንድ ከሚ​ፈ​ል​ጉት ሰዎች ጋራ የጌ​ታ​ችን ከሃ​ሊ​ነት እን​ደ​ሚ​ኖር ለን​ጉሡ ነግ​ረ​ነው ነበ​ርና።

53 ዳግ​መ​ኛም ስለ​ዚህ ሁሉ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለመን፤ እር​ሱም ይቅር አለን።


ለቤተ መቅ​ደስ ሥራ የቀ​ረበ መባእ

54 ከሕ​ዝ​ቡና ከካ​ህ​ናቱ ሹሞች ዐሥራ ሁለ​ቱን ሰዎች፥ ኤሴ​ር​ያ​ንና አሴ​ሚ​ያን፥ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው መካ​ከል ዐሥር ሰዎ​ችን ለየሁ።

55 ንጉ​ሡና መኳ​ን​ንቱ፥ አማ​ካ​ሪ​ዎ​ቹም እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ የሰ​ጡ​ንን ወር​ቁ​ንና ብሩን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቤት ንዋየ ቅድ​ሳት መዝኜ ሰጠ​ኋ​ቸው።

56 ስድ​ስት መቶ አምሳ መክ​ሊት ብርም መዝኜ ሰጠ​ኋ​ቸው።

57 መቶ መክ​ሊት የብር ዕቃ፥ መቶ መክ​ሊ​ትም ወርቅ፥ ሃያ መክ​ሊ​ትም የወ​ርቅ ዕቃ፥ የሚ​ወ​ደድ እንደ ወር​ቅም የጠ​ራና የጠ​ነ​ከረ ዐሥራ ሁለት የናስ ዕቃ መዝኜ ሰጠ​ኋ​ቸው።

58 እን​ዲ​ህም አል​ኋ​ቸው፥ “እና​ን​ተም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተለዩ፥ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ፈጣሪ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስእ​ለት የሆ​ነ​ውን የብ​ሩ​ንና የወ​ር​ቁን ንዋየ ቅድ​ሳ​ትም ለዩ።

59 ለመ​ሳ​ፍ​ን​ቱና ለመ​ኳ​ን​ንቱ፥ ለካ​ህ​ናቱ አለ​ቆ​ችና ለሌ​ዋ​ው​ያኑ፥ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሀገ​ሮች አለ​ቆች በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም በአ​ም​ላ​ካ​ችን ቤት አዳ​ራሽ ውስጥ እስ​ክ​ት​ሰ​ጧ​ቸው ድረስ ተግ​ታ​ችሁ ጠብቁ።”

60 ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያ​ኑም የተ​ቀ​በ​ሉ​ትን ወር​ቁ​ንና ብሩን፥ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም ንዋየ ቅድ​ሳት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ አገቡ።


ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም የተ​መ​ለ​ሱት ሕዝብ

61 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር በዐ​ሥራ ሁለ​ተ​ኛው ቀን ቴራን ከሚ​ባል ሀገር ተነሡ፤ ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችን ሁሉ ባዳ​ነን፥ በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ችን ከእኛ ጋር ባለች ጽን​ዕት እጅም ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ደረሱ።

62 በደ​ረሱ በሦ​ስ​ተ​ኛ​ውም ቀን ወር​ቁ​ንና ብሩን መዝ​ነ​ውና ቈጥ​ረው በቤተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለኦ​ርያ ልጅ ለካ​ህኑ ለመ​ር​ሞ​ቲ​ዮራ ሰጡት።

63 የሁ​ሉም ልኩ፥ ሚዛ​ኑም ያን​ጊዜ ተጻፈ።

64 ከእ​ር​ሱም ጋር የፊ​ን​ሐስ ልጅ አል​ዓ​ዛር ነበረ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር ሌዋ​ው​ያኑ የኢ​ያሱ ልጅ የዘ​ባ​ትና የብኑ ልጅ ሞኢ​ተስ ነበሩ።

65 ከም​ርኮ የተ​መ​ለ​ሱ​ትም ለእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሥ​ዋ​ዕት አቀ​ረቡ። ዐሥራ ሁለት ኮር​ማ​ዎ​ችን፥ ዘጠና ስድ​ስት በጎ​ችን፥

66 ስለ ድኅ​ነ​ትም ሰባ ስድ​ስት ሙክ​ቶ​ችን፥ ዐሥራ ሁለት የበግ ጠቦ​ቶ​ችን፥ ሁሉ​ንም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰዉ።

67 ከዚ​ህም በኋላ ለን​ጉሡ ዕቃ ቤት ሹሞች፥ ለሶ​ር​ያና ለፊ​ንቂ ገዦ​ችም ከን​ጉሡ የመ​ጣ​ውን ደብ​ዳቤ ሰጧ​ቸው፤ ሕዝ​ቡ​ንና የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም መቅ​ደስ አከ​በሩ።


ዕዝራ ከአ​ሕ​ዛብ ጋር የተ​ደ​ረ​ገ​ውን ጋብቻ እንደ ተቃ​ወመ

68 ከዚ​ህም በኋላ ሹሞች መጥ​ተው የሠ​ሩ​ትን ነገ​ሩኝ።

69 እን​ዲ​ህም አሉኝ፥ “የእ​ስ​ራ​ኤል ወገ​ኖች፥ መኳ​ን​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውም፥ ካህ​ኖ​ቻ​ቸ​ውም፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም ከሌ​ሎች የም​ድር አሕ​ዛብ ከከ​ና​ኔ​ዎን፥ ከፌ​ሬ​ዜ​ዎን፥ ከኬ​ጤ​ዎ​ንም፥ ከኢ​ያ​ቡ​ሴ​ዎን፥ ከሞ​ዓ​ባ​ው​ያን፥ ከግ​ብ​ፃ​ው​ያ​ንና ከኤ​ዶ​ሜ​ዎን ርኵ​ሰት አል​ተ​ለ​ዩም።

70 ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ውን አገቡ፤ እነ​ር​ሱና ልጆ​ቻ​ቸ​ውም የከ​በ​ረ​ውን ዘር ከባ​ዕ​ዳን የም​ድር አሕ​ዛብ ጋር ቀላ​ቀሉ፤ መሳ​ፍ​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውና መኳ​ን​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሥራ​ቸው ጀምሮ በዚ​ያች ኀጢ​አት አንድ ሆኑ።”

71 ከዚ​ህም በኋላ ይህን በሰ​ማሁ ጊዜ ልብ​ሴ​ንና ልብሰ ተክ​ህ​ኖ​ዬን ቀደ​ድሁ፤ የራ​ሴን ጠጕ​ርና ጢሜ​ንም ነጨሁ፤ ተክ​ዤና አዝ​ኜም ተቀ​መ​ጥሁ።

72 እኔም በዚ​ያች ኀጢ​አት አዝ​ኜና ተክዤ ተቀ​ምጬ ሳለሁ የእ​ስ​ራ​ኤል ፈጣሪ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ የሚ​ፈሩ ሁሉ ወደ እኔ ተሰ​በ​ሰቡ።

73 ከዚ​ህም በኋላ በሠ​ርኩ መሥ​ዋ​ዕት ጊዜ ጾመኛ እንደ ሆንሁ ልብ​ሴና የክ​ህ​ነት ልብሴ እንደ ተቀ​ደደ ሆኖ ተነ​ሣሁ፤ በጉ​ል​በ​ቴም ተን​በ​ረ​ከ​ክሁ፤ እጆ​ች​ንም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘረ​ጋሁ።

74 እን​ዲ​ህም አልሁ፥ “አቤቱ ጌታዬ ከፊ​ትህ የተ​ነሣ አፍ​ራ​ለሁ፤ እፈ​ራ​ለ​ሁም።

75 ኀጢ​አ​ታ​ችን በዝ​ት​ዋ​ልና፥ ከራ​ሳ​ች​ንም ከፍ ከፍ ብሏ​ልና፥ አለ​ማ​ወ​ቃ​ች​ንም እስከ ሰማይ ደር​ሷ​ልና።

76 ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በታ​ላቅ ኀጢ​አት ላይ ኖረ​ናል።

77 በእኛ ኀጢ​አ​ትና በአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ንም ኀጢ​አት የም​ድር ነገ​ሥ​ታት ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ች​ንና ከን​ጉ​ሦ​ቻ​ችን፥ ከካ​ህ​ኖ​ቻ​ች​ንም ጋር ማረ​ኩን፤ በጦ​ራ​ቸ​ውም ዘረ​ፉን፤ እስከ ዛሬም ድረስ አፈ​ርን።

78 አሁን ግን በዚ​ያች በተ​ቀ​ደ​ሰ​ችው ቦታህ ሥር​ንና ስምን ትተ​ው​ልን ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆይ ቸር​ነ​ትህ በእኛ ላይ በዝታ ተደ​ረ​ገ​ች​ልን።

79 በአ​ን​ተም በአ​ም​ላ​ካ​ችን ቤት ብር​ሃን ተገ​ለ​ጠ​ልን፤ ተገ​ዥ​ዎ​ችም በሆ​ንን ጊዜ ምግ​ባ​ች​ንን ሰጠ​ኸን።

80 በተ​ገ​ዛ​ንም ጊዜ አንተ አም​ላ​ካ​ችን አል​ተ​ው​ኸ​ንም፤ በፋ​ርስ ነገ​ሥ​ታ​ትም ፊት ሞገ​ስን ሰጠ​ኸን፤ ምግ​ባ​ች​ንን ይሰ​ጡን ዘንድ፥

81 ቤተ መቅ​ደ​ሳ​ች​ን​ንም ያከ​ብሩ ዘንድ፥ የጽ​ዮ​ን​ንም ፍራ​ሿን ይሠሩ ዘንድ፥ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ኀይ​ልን ይሰ​ጡን ዘንድ አል​ተ​ው​ኸ​ንም።

82 “አቤቱ፥ አሁ​ንስ ይህ በእኛ ላይ ሳለ ምን እን​ላ​ለን? በባ​ሮ​ችህ በነ​ቢ​ያ​ትም እጅ እን​ዲህ ስትል የሰ​ጠ​ኸ​ውን ትእ​ዛ​ዝ​ህን ካድን።

83 ትወ​ር​ሷት ዘንድ ወደ እርሷ ትገ​ባ​ላ​ችሁ ያል​ሃ​ቸው ያች ምድር በም​ድር አሕ​ዛብ ርኵ​ሰት የተ​ዳ​ደ​ፈች ምድር ናት፤ ርኵ​ሰ​ታ​ቸ​ው​ንም መሏት።

84 ሴቶች ልጆ​ቻ​ች​ሁን ለወ​ን​ዶች ልጆ​ቻ​ቸው አታ​ጋቡ፤ ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ለወ​ን​ዶች ልጆ​ቻ​ችሁ አታ​ጋቡ፤

85 ድል ትነ​ሷ​ቸው ዘንድ፥ የም​ድ​ር​ንም በረ​ከት ትበሉ ዘንድ፥ ለል​ጆ​ቻ​ችሁ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ታወ​ር​ሷት ዘንድ በዘ​መ​ና​ችሁ ሁሉ ከእ​ነ​ርሱ ጋር አት​ስ​ማሙ።

86 ይህ​ችም ያገ​ኘ​ችን ሁሉ ስለ ሥራ​ችን ክፋ​ትና ስለ ኀጢ​አ​ታ​ችን ብዛት ነው።

87 አቤቱ አንተ ግን ኀጢ​አ​ታ​ች​ንን ታገ​ሥህ፤ እን​መ​ለ​ስም ዘንድ ሥርን ሰጠ​ኸን፤ ዳግ​መ​ኛም ሕግ​ህን አፍ​ር​ሰን ከም​ድር አሕ​ዛብ ርኩ​ሰት ጋር አንድ እን​ሆን ዘንድ ይገ​ባ​ና​ልን?

88 ብት​ቈ​ጣ​ንስ ሥር​ንና ዘርን፥ ስማ​ች​ን​ንም እስ​ከ​ማ​ታ​ስ​ቀር ድረስ ባጠ​ፋ​ኸን ነበር።

89 አቤቱ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ አንተ፥ እው​ነ​ተኛ ነህ፥ ዛሬ ሥርን ትተ​ህ​ል​ና​ልና።

90 አሁ​ንም በፊ​ትህ በኀ​ጢ​አ​ታ​ችን አለን። ስለ​ዚህ በፊ​ትህ እን​ቆም ዘንድ አይ​ገ​ባ​ንም።”

91 ዕዝ​ራም በቤተ መቅ​ደሱ አን​ጻር ተን​በ​ር​ክኮ እያ​ለ​ቀሰ በጸ​ለ​የና በተ​ና​ዘዘ ጊዜ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያሉ ብዙ ሰዎች ሴቶ​ችና ወን​ዶች፥ ቆነ​ጃ​ጅ​ቱም ወደ እርሱ ተሰ​በ​ሰቡ፤ በሁ​ሉም ላይ ታላቅ ልቅሶ ሆነ።

92 ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ውስጥ የኢ​ያ​ኤል ልጅ ኢኮ​ን​ያስ ዕዝ​ራን ጠርቶ እን​ዲህ አለው፥ “ልዩ ከሚ​ሆኑ ከም​ድር አሕ​ዛብ ወገን ሚስት ያገ​ባን እኛ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በድ​ለ​ናል፤ አሁ​ንም ይህ ሁሉ በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ አለ።

93 ነገር ግን እንደ ፍር​ድህ ልዩ ከሚ​ሆኑ ከም​ድር አሕ​ዛብ ወገን ያገ​ባ​ና​ቸ​ውን ሚስ​ቶ​ቻ​ች​ንን ሁሉ ከል​ጆ​ቻ​ቸው ጋራ ከእኛ እና​ስ​ወ​ጣ​ቸው ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም እን​ማ​ማል።

94 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ የሚ​ወዱ ሰዎ​ች​ንም ሁሉ ተነ​ሥ​ተህ አም​ላ​ቸው።

95 ይህ ሥራ ባንተ ላይ ነውና፥ እኛም ካንተ ጋር ነንና፥ እን​ረ​ዳ​ሃ​ለ​ን​ምና።”

96 ዕዝ​ራም ተነ​ሥቶ የሕ​ዝ​ቡን ሹሞ​ችና ካህ​ና​ቱን፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑ​ንም፥ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ሁሉ እን​ዲሁ ያደ​ርጉ ዘንድ አማ​ላ​ቸው፤ እነ​ር​ሱም ማሉ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos