Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ካልእ 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የቤተ መቅ​ደሱ ቅዳሴ

1 ከዚ​ህም በኋላ የቄሌ-ሶር​ያና የፊ​ን​ቂስ ገዥ ሲሳ​ኒ​ስና፥ ሳት​ራ​ቡ​ዛ​ኒስ፥ ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ንጉሡ ዳር​ዮስ እን​ዳ​ዘዘ ይሠሩ ዘንድ ጀመሩ።

2 እነ​ር​ሱም ተግ​ተው ከአ​ይ​ሁድ ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ጋር ቆመው ያዝዙ ነበር።

3 የቤተ መቅ​ደ​ሱም ሥራ፥ ነቢ​ያቱ ሐጌና ዘካ​ር​ያስ ትን​ቢት እየ​ተ​ና​ገ​ሩ​ላ​ቸው ፈጥኖ ተከ​ና​ወነ።

4 በፋ​ርስ ነገ​ሥ​ታት በቂ​ሮ​ስና ዳር​ዮስ፥ በአ​ር​ጤ​ክ​ስ​ስም ፈቃድ በእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ ሥራ​ውን ፈጸሙ።

5 ቤተ መቅ​ደሱ አዳር በሚ​ባል ወር በጨ​ረቃ በስ​ም​ን​ተ​ኛው ቀን በዳ​ር​ዮስ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥት ተፈ​ጸመ።

6 የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆ​ችና ካህ​ናት፥ ሌዋ​ው​ያ​ንም፥ ከም​ርኮ የተ​መ​ለ​ሱት ሕዝ​ቡም ሁሉ በሙሴ መጽ​ሐፍ እንደ ተጻፈ ሥር​ዐ​ቱን አደ​ረጉ።

7 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ ቅዳ​ሴም ቤት መቶ ኮር​ማ​ዎ​ችን፥ ሁለት መቶ ፍየ​ሎ​ችና አራት መቶ በጎ​ችን አቀ​ረቡ።

8 ስለ እስ​ራ​ኤ​ልም ኀጢ​አት ሁሉ ማስ​ተ​ስ​ረያ፦ ባሥራ ሁለቱ ነገደ እስ​ራ​ኤል ሹሞች ቍጥር ዐሥራ ሁለት ሙክ​ቶ​ችን አቀ​ረቡ።

9 ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያ​ኑም በሙሴ መጽ​ሐፍ እንደ ተጻፈ እንደ ሥር​ዐ​ታ​ቸው ለእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ግ​ሎት በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ልብሰ ተክ​ህ​ኖ​ውን ለብ​ሰው ቆሙ። በረ​ኞ​ችም በየ​በ​ሮ​ቻ​ቸው ቆሙ።


የፋ​ሲካ በዓል

10 ከም​ርኮ የተ​መ​ለሱ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆ​ችም በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር በዐ​ሥራ አራ​ተ​ኛው ቀን የፋ​ሲ​ካን በዓል አከ​በሩ። ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያኑ፥ ሁሉም ራሳ​ቸ​ውን በአ​ን​ድ​ነት አን​ጽ​ተ​ዋ​ልና።

11 ከም​ርኮ የተ​መ​ለ​ሱት ልጆ​ቻ​ቸው ግን ሁሉም ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን አላ​ነ​ጹም ነበር፤ ሌዋ​ው​ያን ግን ሁሉም ነጽ​ተው ነበ​ርና፤

12 ከም​ርኮ ለተ​መ​ለ​ሱት ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ለካ​ህ​ና​ትና ለራ​ሳ​ቸ​ውም የፋ​ሲ​ካን በግ ሠዉ።

13 ከም​ርኮ የተ​መ​ለሱ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ሁሉ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ይሹት ዘንድ ከም​ድር አሕ​ዛብ ርኵ​ሰት የተ​ለ​ዩት ሁሉ ፋሲ​ካ​ውን በሉ።

14 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ደስ ብሏ​ቸው ሰባት ቀን የቂ​ጣ​ዉን በዓል አከ​በሩ።

15 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የፋ​ር​ሱን ንጉሥ ልቡና መል​ሶ​ላ​ች​ዋ​ልና፥ ለእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራም እጃ​ቸ​ውን አጽ​ን​ቶ​ላ​ቸ​ዋ​ልና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos