መዝሙር 150 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉምእግዚአብሔርን አመስግኑ! 1 እግዚአብሔርን አመስግኑ! እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት! የሚያስደንቅ ኀይሉ ባለበት በሰማይ አመስግኑት! 2 ስላደረገው ድንቅ ሥራ አመስግኑት፤ ወደር ስለማይገኝለት ታላቅነቱ አመስግኑት። 3 በመለከት አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት። 4 በከበሮና በማሸብሸብ አመስግኑት፤ በክራርና በዋሽንት አመስግኑት። 5 በጸናጽል ድምፅ አመስግኑት፤ ከፍተኛ ድምፅ ባለው ጸናጽል አመስግኑት። 6 ሕያዋን ፍጥረቶች ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑት! እግዚአብሔር ይመስገን! |