Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 124 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም


እግዚአብሔር ወገኖቹን የሚጠብቅ መሆኑ

1 እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ባይሆን ምን ይበጀን ነበር? እስራኤል እንዲህ ብሎ ይመልስ፤

2 “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ባይሆን ጠላቶቻችን ባጠቁን ጊዜ

3 በታላቅ ቊጣ በእኛ ላይ ተነሥተው ከነሕይወታችን በዋጡን ነበር፤

4 ጐርፍ በወሰደን፥ ውሃም በሸፈነን ነበር፤

5 ብርቱ ማዕበልም ባሰጠመን ነበር።”

6 ጠላቶቻችን እንዲደመስሱን ያላደረገ እግዚአብሔር ይመስገን።

7 እንደ ወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አምልጠናል፤ ወጥመዱ ተሰበረ፤ እኛም ነጻ ወጣን።

8 ይህንንም ርዳታ ያገኘነው ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

© The Bible Society of Ethiopia, 2005

© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997

Bible Society of Ethiopia
Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos