መዝሙር 113 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉምየእግዚአብሔርን ቸርነት የሚገልጥ ምስጋና 1 እግዚአብሔር ይመስገን! እናንተ የእግዚአብሔር አገልጋዮች የእግዚአብሔርን ስም አመስግኑ! 2 አሁንም ለዘለዓለም ስሙ ይመስገን። 3 ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያዋ ድረስ የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን! 4 እግዚአብሔር የመንግሥታት ሁሉ ገዢ ነው፤ ክብሩም ከሰማያት ሁሉ በላይ ነው። 5 እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም፤ ዙፋኑም ከሁሉ በላይ ነው። 6 ነገር ግን ሰማይንና ምድርን ወደ ታች ይመለከታል። 7 ድኾችን ከትቢያ ችግረኞችንም ከዐመድ ቊልል ያነሣቸዋል። 8 የልዑላን ጓደኞች ያደርጋቸዋል፤ ከሕዝቡም አለቆች ጋር ያስቀምጣቸዋል። 9 መኻኒቱንም በቤቷ በክብር ያኖራታል፤ ልጆችንም በመስጠት ደስ ያሰኛታል። እግዚአብሔር ይመስገን! |