Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዘሌዋውያን INTRO1 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

1

መግቢያ
ኦሪት ዘሌዋውያን የሚያትተው በጥንታዊት እስራኤል ስለ ነበሩት የአምልኮ ደንቦችና ስለ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው፤ እንዲሁም እነዚህን ሥርዓቶች በተግባር የመተርጐም ኀላፊነት ስለ ነበራቸው ካህናት ይገልጣል።
የመጽሐፉ ማእከላዊ ሐሳብ ስለ እግዚአብሔር ቅድስና የሚናገር ነው፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር ሕዝብ ከዚሁ ቅዱስ ከሆነው ከእስራኤል አምላክ ጋር የቅርብ ግንኙነት ይኖራቸው ዘንድ፥ በእንዴት ያለ ሁኔታ ማምለክ እንደሚገባቸው ይዘረዝራል።
ከመጽሐፉ ውስጥ በጣም የታወቀው ትእዛዝ ኢየሱስ ሁለተኛው ታላቅ ትእዛዝ ብሎ የሠየመውና በም. 19 ቊ. 18 ላይ የሚገኘው ነው፤ እርሱም “ሰውን ሁሉ እንደ ራስህ አድርገህ ውደድ” የሚለው ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
ሀ. የመባና የመሥዋዕት ሕግ 1፥1—7፥38
ለ. የአሮንና የልጆቹ የክህነት ሹመት 8፥1—10፥20
ሐ. ንጹሕ የሆነና ያልሆነ ነገር፥ እንዲሁም የመንጻት ሥርዓት 11፥1—15፥33
መ. የኃጢአት ስርየት ቀን 16፥1-34
ሠ. የቅድስና ሕይወትና የአምልኮ ሕግ 17፥1—27፥34

© The Bible Society of Ethiopia, 2005

© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997

Bible Society of Ethiopia
Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos