ሐጌ INTRO1 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉምመግቢያ በትንቢተ ሐጌ የተጠናቀሩት አጫጭር መልእክቶች እግዚአብሔር ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስት መቶ ዓመት በነቢዩ ሐጌ አማካይነት ያስተላለፋቸው ናቸው። ሕዝቡ ከስደት ተመልሰው በኢየሩሳሌም መኖር ከጀመሩ ጥቂት ዓመቶች ያለፋቸው ቢሆንም እንኳ ቤተ መቅደሱ ገና እንደ ፈረሰ ነበር፤ ስለዚህ መልእክቱ የሕዝቡ መሪዎች ቤተ መቅደሱን እንዲያድሱ የሚገፋፋ ነበር፤ ሕዝቡ ተሐድሶና ንጽሕና የሚኖራቸው ከሆነም፥ እግዚአብሔር ወደ ፊት ሰላምና ብልጽግና እንደሚሰጣቸው ይናገራል። አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት 1. ጌታ ቤተ መቅደሱ እንዲሠራ ማዘዙ 1፥1-15 2. ጌታ ለሕዝቡ የሰጠው የበረከትና የማጽናናት ተስፋ 2፥1-19 3. እግዚአብሔር ዘሩባቤል የሰጠው ተስፋ 2፥20-23 |