Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -


This book is not inspired by God and is not part of the Christian canon or the Jewish Tanakh. It is shown only for historical and study purposes. View full explanation

መጽሐፈ ሲራክ 50 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የኦ​ንያ ልጅ ስም​ዖን

1 የኦ​ንያ ልጅ ታላቁ ካህን ስም​ዖ​ንም በሕ​ይ​ወቱ ቤተ መቅ​ደ​ስን አደሰ፤ በዘ​መ​ኑም ቤተ መቅ​ደ​ስን አጸና።

2 እን​ዲ​ሁም የቅ​ጥ​ሩን መሠ​ረት ዕጥፍ አድ​ርጎ ሠራ ካህን የሚ​ለ​ብ​ሰ​ው​ንም ቀጭን ልብስ ሠራ።

3 በዘ​መ​ኑም የው​ኃ​ዎች ምን​ጮች አል​ጐ​ደ​ሉም፤ የጕ​ድ​ጓ​ዱም ውኃ ብዛቱ እንደ ባሕር ውኃ ነበር።

4 ሕዝ​ቡም እን​ዳ​ይ​ወ​ድቁ ይጠ​ነ​ቀ​ቅ​ላ​ቸው ነበር፤ ከተ​ማ​ዋ​ንም ከጠ​ላት ለመ​ከ​ላ​ከል መሸገ።

5 ከቤተ መቅ​ደስ መጋ​ረጃ በወጣ ጊዜም በሕ​ዝቡ መካ​ከል ተከ​በረ።

6 በደ​መና ውስጥ እንደ አጥ​ቢያ ኮከ​ብና በም​ል​ዐት ቀን እንደ ሙሉ ጨረቃ ነበረ።

7 በል​ዑል መቅ​ደ​ስም ላይ እን​ደ​ም​ታ​በራ ፀሐይ ነበረ። በብ​ሩህ ደመ​ናም ውስጥ ብር​ሃን እን​ደ​ሚ​ሰጥ ቀስተ ደመና ነበር።

8 እንደ መጸው ወራት ጽጌ​ረ​ዳም ነበር፤ በውኃ መፍ​ሰሻ አጠ​ገብ እን​ደ​ሚ​ያ​ፈራ አበ​ባም ነበር፤ በመ​ከ​ርም ወራት እንደ ሊባ​ኖስ ዛፍ ቅር​ን​ጫፍ ነበር።

9 በጥና እሳት ላይ እን​ዳለ ነጭ ዕጣ​ንም ነበር። ተመ​ትቶ እንደ ተሠራ የወ​ርቅ ዕቃም ነበር። በጌጥ ላይ እን​ዳለ የከ​በረ ዕን​ቍም ነበር፤

10 ፍሬዋ ብዙ እንደ ሆነ የዘ​ይት እን​ጨት፥ ከደ​መና በታች እን​ደ​ሚ​ያ​ድግ የዋ​ንዛ ዛፍ ነበር።

11 እር​ሱም የክ​ብር ልብ​ሱን በለ​በሰ ጊዜ፥ የመ​መ​ኪ​ያ​ው​ንም ጌጥ በለ​በሰ ጊዜ፥ ወደ ተቀ​ደ​ሰ​ውም መሠ​ዊያ በወጣ ጊዜ፥ በቅ​ድ​ስና ልብሱ ተከ​በረ።

12 ከካ​ህ​ና​ቱም እጅ የመ​ሥ​ዋ​ዕ​ቱን ሥጋ ክፍል በተ​ቀ​በለ ጊዜ፥ በመ​ሠ​ዊ​ያው አጠ​ገብ ይቆም ነበር፤ ወን​ድ​ሞ​ቹም በዙ​ሪ​ያው ቁመው ይጋ​ር​ዱት ነበር፤ እንደ ሊባ​ኖስ ለጋ ዝግ​ባና እንደ ዘን​ባ​ባም ዛፍ ይከ​ቡት ነበር።

13 እን​ዲ​ሁም የአ​ሮን ልጆች ሁሉ የክ​ብር ልብ​ሳ​ቸ​ውን ለብ​ሰው፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መባእ በእ​ጃ​ቸው ይዘው፥ በእ​ስ​ራ​ኤል ማኅ​በር ሁሉ ፊት ይቆሙ ነበር።

14 በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ሥራ​ቸ​ውን ይፈ​ጽሙ ነበር፤ ሁሉን የሚ​ችል የል​ዑ​ል​ንም መሥ​ዋ​ዕት ያዘ​ጋጁ ነበር።

15 የወ​ይ​ኑን ጽዋዕ ይዞ እጁን አነሣ፤ የወ​ይ​ኑን ዘለላ ደምም አፈ​ሰሰ፤ ለን​ጉሠ ነገ​ሥት ለል​ዑል በጎ መዓዛ አድ​ርጎ በመ​ሠ​ዊ​ያው እግር ሥር ያፈ​ስ​ሰው ነበር።

16 የአ​ሮ​ንም ልጆች እየ​ጮሁ ምስ​ጋ​ና​ውን ይና​ገሩ ነበር፤ ተመ​ትቶ የተ​ሠራ የብር መለ​ከ​ት​ንም ይነፉ ነበር፤ በል​ዑ​ልም ፊት ማሰ​ባ​ሰ​ቢያ ሊሆን ቃላ​ቸ​ውን ያሰሙ ነበር።

17 ያን ጊዜም ሕዝቡ ሁሉ በአ​ን​ድ​ነት ያርፉ ነበር፤ በም​ድር ላይም በግ​ን​ባ​ራ​ቸው ይሰ​ግዱ ነበር፤ ሁሉን ለሚ​ገዛ ለል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ምስ​ጋና ያቀ​ርቡ ነበር።

18 መዘ​ም​ራ​ኑም በቃ​ላ​ቸው ያመ​ሰ​ግ​ኑት ነበር፥ የዜ​ማ​ቸ​ውም ድምፅ ቤቱን ያስ​ተ​ጋ​ባው ነበር።

19 ሕዝ​ቡም ወደ ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይጸ​ልዩ ነበር፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ጸን​ተው ሥር​ዐ​ቱን እስ​ኪ​ጨ​ርሱ ድረስ ይቅር በሚል በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ይለ​ምኑ ነበር፤ ሥር​ዐ​ቱ​ንም ያከ​ና​ውኑ ነበር።

20 ከዚ​ህም በኋላ እርሱ ወርዶ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በረ​ከት በአ​ን​ደ​በቱ ይሰ​ጣ​ቸው ዘንድ፥ በስ​ሙም ይመኩ ዘንድ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ማኅ​በር ሁሉ ላይ እጁን አነሣ።

21 የል​ዑ​ል​ንም በረ​ከት ይቀ​በሉ ዘንድ ዳግ​መኛ ሰገዱ።

22 አሁ​ንም በሁ​ሉም ቦታ ብዙ ተአ​ም​ራት የሚ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን፥ ከእ​ና​ታ​ችን ማኅ​ፀን ጀምሮ ዘመ​ና​ች​ን​ንም የሚ​ያ​ረ​ዝ​መ​ውን፥ እንደ ቸር​ነ​ቱም ይቅ​ር​ታ​ውን የሚ​ያ​ደ​ር​ግ​ል​ንን፥ የሁ​ሉን ፈጣሪ አመ​ስ​ግ​ኑት።

23 የል​ቡና ደስ​ታ​ንም ይሰ​ጠ​ናል፤ በዘ​መ​ና​ች​ንም ሰላ​ምን ያደ​ር​ጋል፤ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ለዘ​ለ​ዓ​ለም።

24 በቸ​ር​ነ​ቱም ከእኛ ጋር የታ​መነ ነው፤ በዘ​መ​ና​ች​ንም አዳ​ነን።

25 ሰው​ነቴ ሁለት ወገ​ኖ​ችን ጠላች፤ ሦስ​ተ​ኛው ግን ሕዝብ አይ​ደ​ለም።

26 እነ​ዚ​ህም በሰ​ማ​ር​ያና በፍ​ል​ስ​ጥ​ኤም ተራራ የሚ​ኖሩ፥ በሰ​ቂማ የሚ​ኖሩ የአ​ሞ​ሬ​ዎ​ንም ሰዎች ናቸው።

27 ጥበ​ብን ከልቡ ያነ​ቃት የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ሰው የሲ​ራክ አል​ዓ​ዛር ልጅ እኔ ኢያሱ የጥ​በ​ብ​ንና የም​ክ​ርን ትም​ህ​ርት በዚህ መጽ​ሐፍ ጻፍሁ።

28 ይህን እን​ደ​ዚህ የሚ​ያ​ደ​ርግ፥ በዚ​ያም የሚ​ራ​ቀቅ ብፁዕ ነው፤ ይህ​ንም በልቡ የሚ​ጠ​ብ​ቀው ጠቢብ ይሆ​ናል።

29 ይህ​ንም የሚ​ያ​ደ​ርግ ሁሉን ይች​ላል፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብር​ሃን ይመ​ራ​ዋ​ልና።

Follow us:



Advertisements