Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -


This book is not inspired by God and is not part of the Christian canon or the Jewish Tanakh. It is shown only for historical and study purposes. View full explanation

መጽሐፈ ሲራክ 49 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ንጉሡ ኢዮ​ስ​ያስ

1 የኢ​ዮ​ስ​ያስ መታ​ሰ​ቢ​ያው በቀ​ማሚ ብል​ሃት እንደ ተቀ​መመ ሽቱ ነው፤ እንደ ማርም በአፍ ሁሉ ጣፋጭ ነው፤ በመ​ጠጥ ግብ​ዣም ጊዜ እንደ ዘፈን ነው።

2 እርሱ የቀና ነው፤ ሕዝ​ቡ​ንም መለ​ሳ​ቸው፤ የኀ​ጢ​አ​ት​ንም ርኵ​ሰት ሁሉ አስ​ወ​ገደ።

3 ልቡ​ና​ው​ንም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አቀና፤ በኃ​ጥ​ኣ​ንም ዘመን ጽድ​ቅን አጸ​ናት።

4 ከዳ​ዊት፥ ከሕ​ዝ​ቅ​ያ​ስና ከኢ​ዮ​ስ​ያስ በቀር ሁሉም በድ​ለ​ዋል፤ የል​ዑ​ልን ሕግ ትተ​ዋ​ልና፤ የይ​ሁ​ዳም ነገ​ሥ​ታት አለቁ።

5 ኀይ​ላ​ቸ​ውን ለሌላ ሰጥ​ተ​ዋ​ልና፥ ክብ​ራ​ቸ​ው​ንም ለሌላ ሕዝብ ሰጥ​ተ​ዋ​ልና።


ነቢዩ ኤር​ም​ያስ

6 የተ​መ​ረ​ጠ​ች​ው​ንና የተ​ቀ​ደ​ሰ​ች​ውን ከተማ አቃ​ጠ​ሏት። መከራ አጽ​ን​ተ​ው​ባ​ታ​ልና እንደ ነቢዩ ኤር​ም​ያስ ትን​ቢት ጎዳ​ና​ዋን አጠፉ።

7 አሠ​ቃ​ይ​ተ​ው​ታ​ልና፤ እርሱ ግን ነቢይ ይሆን ዘንድ፥ ይነ​ቅል ዘንድ፥ ያጠ​ፋም ዘንድ፥ እን​ደ​ዚ​ሁም ይተ​ክል ዘንድ፥ ይሠ​ራም ዘንድ በእ​ናቱ ማኅ​ፀን ተመ​ረጠ።


ነቢዩ ሕዝ​ቅ​ኤል

8 ሕዝ​ቅ​ኤ​ልም የጌ​ት​ነ​ቱን ራእይ አየ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም በኪ​ሩ​ቤል ሠረ​ገላ ላይ አየው።

9 ጠላ​ቶ​ቹ​ንም በመ​ዓት ዐሰ​ባ​ቸው፥ የጻ​ድ​ቃ​ን​ንም ጎዳ​ና​ቸ​ውን በመ​ል​ካም አቀና።

10 የዐ​ሥራ ሁለቱ ነቢ​ያ​ትም አጽ​ሞ​ቻ​ቸው በየ​ቦ​ታ​ቸው ለመ​ለሙ፤ ያዕ​ቆ​ብን አጽ​ና​ን​ተ​ው​ታ​ልና፥ በታ​መነ ተስ​ፋም አድ​ነ​ው​ታ​ልና።

11 ዘሩ​ባ​ቤ​ልን እን​ዴት እና​ገ​ን​ነው ይሆን! እር​ሱስ በቀኝ እጅ እን​ዳለ እንደ ሐቲም ቀለ​በት ነው።

12 የዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ ዮሴ​ዕም እን​ዲሁ ነበረ፤ በዘ​መ​ና​ቸ​ውም ቤተ መቅ​ደ​ስን ሠሩ፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ክብር የተ​ዘ​ጋጀ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሕዝብ አከ​በ​ሩት።

13 የነ​ሕ​ም​ያም መታ​ሰ​ቢ​ያው ብዙ ነው፤ የወ​ደ​ቀ​ች​ውን ቅጽር አነ​ሣ​ልን፤ ደጃ​ፎ​ች​ንም አቆ​መ​ልን፤ ቍል​ፍ​ንም ሠራ​ልን፥ ቤታ​ች​ን​ንም ገነ​ባ​ልን።

14 እንደ ሄኖክ ያለ ሰው በም​ድር የተ​ፈ​ጠረ የለም፤ እርሱ ከዚህ ዓለም ተወ​ሰደ።

15 እንደ ዮሴ​ፍም ያለ ሰው አል​ተ​ወ​ለ​ደም፤ ለወ​ን​ድ​ሞቹ አለቃ ሆነ፤ ለሕ​ዝ​ቡም ኀይል ሆነ፥ ለአ​ጽ​ሞ​ቹም ይቅ​ር​ታን አገኘ።

16 ሴምና ሴት ከሰው ይልቅ ከበሩ፥ አዳ​ምም ከተ​ፈ​ጠ​ረው ሕያው ፍጥ​ረት ሁሉ ከበረ፤

Follow us:



Advertisements