ዘኍል 31:5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)5 ከእስራኤልም አእላፋት፥ ከየነገዱ አንድ አንድ ሺህ ቈጠሩ፤ ለጦርነት የተሰለፉትም ዐሥራ ሁለት ሺህ ሆኑ። See the chapterአዲሱ መደበኛ ትርጒም5 ስለዚህ ከእስራኤል ጐሣዎች ተወጣጥቶ ከእያንዳንዱ ነገድ አንድ ሺሕ፣ በአጠቃላይ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ሰው ለጦርነት ተዘጋጀ። See the chapterመጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)5 ከብዙ ሺህ እስራኤላውያን መካከል ዐሥራ ሁለት ሺህ፥ ከየነገዱ አንድ አንድ ሺህ፥ ለጦርነት የተዘጋጁ ሰዎች ተመለመሉ። See the chapterአማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም5 ስለዚህ ከብዙ ሺህ እስራኤላውያን መካከል ከያንዳንዱ ነገድ አንዳንድ ሺህ ተውጣጥቶ ዐሥራ ሁለት ሺህ የታጠቀ ሠራዊት ለጦርነት ተዘጋጀ። See the chapterመጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)5 ከእስራኤልም አእላፋት አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከየነገዱ አንድ አንድ ሺህ፥ ለጦርነት የተሰለፉ ሰዎች ተሰጡ። See the chapter |