Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




ኢያሱ 11:16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

16 ኢያ​ሱም ያን ምድር ሁሉ፥ ተራ​ራ​ማ​ውን፥ ደቡ​ቡ​ንም ሁሉ፥ የጎ​ሶ​ም​ንም ምድር ሁሉ ፥ ሜዳ​ው​ንም፥ በም​ዕ​ራብ በኩል ያለ​ው​ንም፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ተራ​ራ​ማ​ው​ንና ቆላ​ውን ያዘ፤

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

16 ኢያሱ ያን ምድር በሙሉ፣ ማለት ተራራማውን አገር፣ ኔጌብን ሁሉ፣ የጎሶምን ምድር በሙሉ፣ የምዕራቡን ቈላ፣ ዓረባን እንዲሁም የእስራኤልን አገር ደጋውንና ቈላውን ጠቅልሎ ያዘ፤

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

16 ኢያሱም ያን ምድር ሁሉ፥ ተራራማውን፥ ደቡቡንም ሁሉ፥ የጎሶምንም ምድር ሁሉ፥ ቈላውንም፥ ዓረባንም፥ የእስራኤልንም ተራራማውንና ቈላውን ያዘ፥

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

16 ኢያሱ እነዚያን አገሮች፦ ተራራማውን፥ ኔጌብን፥ የጎሼንን ምድር፥ ቈላማውን፥ የዮርዳኖስን ሸለቆ፥ ቈላማውንና ደጋማውን የእስራኤልን ምድር ሁሉ ያዘ።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

16 ኢያሱም ያን ምድር ሁሉ፥ ተራራማውን፥ ደቡቡንም ሁሉ፥ የጎሶምንም ምድር ሁሉ፥ ቈላውንም፥ ዓረባንም፥ የእስራኤልንም ተራራማውንና ቈላውን ያዘ፥

See the chapter Copy




ኢያሱ 11:16
16 Cross References  

ኢያ​ሱም ከቃ​ዴስ በርኔ እስከ ጋዛ ድረስ፥ የጎ​ሶ​ም​ንም ምድር ሁሉ እስከ ገባ​ዖን ድረስ መታ።


በተ​ራ​ራና በሜዳ በዓ​ረባ፥ በአ​ሴ​ዶት በቆ​ላው፥ በና​ጌብ፥ በኬ​ጤ​ዎ​ንና በአ​ሞ​ሬ​ዎን፥ በከ​ና​ኔ​ዎ​ንና በፌ​ር​ዜ​ዎን፥ በኢ​ያ​ቡ​ሴ​ዎ​ንና በኤ​ዌ​ዎን ያለ ርስ​ታ​ቸ​ውን አወ​ረ​ሳ​ቸው።


በዚያ ጊዜም ኢያሱ ሄደ፤ በተ​ራ​ራ​ማ​ውም ሀገር የሚ​ኖሩ ኤና​ቃ​ው​ያ​ንን ከኬ​ብ​ሮ​ንና ከዳ​ቤር፥ ከአ​ና​ቦ​ትም፥ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ተራራ ሁሉ፥ ከይ​ሁ​ዳም ተራራ ሁሉ አጠ​ፋ​ቸው፤ ኢያ​ሱም ከከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው ጋር ፈጽሞ አጠ​ፋ​ቸው።


“የእ​ስ​ራ​ኤል ተራ​ሮች ሆይ! ሕዝቤ ይመጡ ዘንድ ተስፋ ያደ​ር​ጋ​ሉና ወይ​ና​ች​ሁ​ንና ፍሬ​ያ​ች​ሁን ይበ​ላሉ።


ከፍ ባለው በእ​ስ​ራ​ኤል ተራራ ላይ እተ​ክ​ለ​ዋ​ለሁ፤ ቅር​ን​ጫ​ፎ​ች​ንም ያወ​ጣል፤ ፍሬም ያፈ​ራል፤ ታላ​ቅም ዝግባ ይሆ​ናል፤ በበ​ታ​ቹም ወፎች ሁሉ ያር​ፋሉ፤ በቅ​ር​ን​ጫ​ፎ​ቹም ጥላ በክ​ንፍ የሚ​በ​ርር ሁሉ ይጠ​ጋል፤ ቅር​ን​ጫ​ፉም ይሰ​ፋል።


በመ​ስ​ዕም በተ​ራ​ራ​ማው ሀገር ፥ በከ​ነ​ሬ​ትም ዐዜብ በዓ​ረባ፥ በቆ​ላ​ውም ባለ በፊ​ና​ዶር ሸለቆ ወደ ነበሩ ነገ​ሥ​ታት፥


እን​ዲ​ህም ሆነ፤ በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ በተ​ራ​ራ​ማው በሜ​ዳ​ውም በታ​ላቁ ባሕር ዳር በሊ​ባ​ኖ​ስም ፊት ለፊት የነ​በሩ ነገ​ሥት ሁሉ፥ ኬጤ​ዎ​ና​ዊዉ፥ አሞ​ሬ​ዎ​ና​ዊ​ዉም፥ ከነ​ዓ​ና​ዊ​ዉም፥ ፌር​ዜ​ዎ​ና​ዊ​ዉም፥ ኤዌ​ዎ​ና​ዊ​ዉም፥ ኢያ​ቡ​ሴ​ዎ​ና​ዊ​ዉም፥ ጌር​ጌ​ሴ​ዎ​ና​ዊ​ዉም ይህን በሰሙ ጊዜ፥


እን​ዲ​ሁም ኢያሱ ምድ​ሪ​ቱን ሁሉ፥ ተራ​ራ​ማ​ውን ሀገር፥ ደቡ​ቡ​ንም፥ ቆላ​ው​ንም፥ ቍል​ቍ​ለ​ቱ​ንም፥ ንጉ​ሦ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሁሉ መታ፤ ማን​ንም አላ​ስ​ቀ​ረም፤ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዘ​ውም ነፍስ ያለ​በ​ትን ሁሉ ፈጽሞ አጠፋ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አገ​ል​ጋ​ዩን ሙሴን እን​ዳ​ዘዘ እን​ዲሁ ሙሴ ኢያ​ሱን አዝ​ዞት ነበር፤ ኢያ​ሱም እን​ዲሁ አደ​ረገ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን ካዘ​ዘው ሁሉ ምንም አላ​ስ​ቀ​ረም።


እንደ ተጨ​ነ​ቁም ተመ​ለ​ከ​ታ​ቸው፥ ጸሎ​ታ​ቸ​ው​ንም ሰማ​ቸው፤


ተመ​ል​ሳ​ችሁ ተጓዙ፤ ወደ አሞ​ራ​ው​ያን ተራራ፥ ወደ አረ​ባም ሀገ​ሮች ሁሉ፥ በተ​ራ​ራ​ውም፥ በሜ​ዳ​ውም፥ በሊ​ባም፥ በባ​ሕ​ርም ዳር ወዳሉ ወደ ከነ​ዓ​ና​ው​ያን ምድር፥ ወደ ሊባ​ኖ​ስም ፊት ለፊት እስከ ታላቁ ወንዝ እስከ ኤፍ​ራ​ጥስ ድረስ ሂዱ።


Follow us:

Advertisements


Advertisements