Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




ኤርምያስ 4:28 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

28 ስለ​ዚህ ምድር ታለ​ቅ​ሳ​ለች፤ በላ​ይም ሰማይ ይጠ​ቍ​ራል፤ ተና​ግ​ሬ​አ​ለ​ሁና፤ አል​ጸ​ጸ​ትም ወደ​ፊት እሮ​ጣ​ለሁ፤ ከእ​ር​ስ​ዋም አል​መ​ለ​ስም።

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

28 ስለዚህ ምድር ታለቅሳለች፤ ሰማያትም በላይ ይጨልማሉ፤ ተናግሬአለሁ፤ ሐሳቤን አልለውጥም፤ ወስኛለሁ፤ ወደ ኋላም አልልም።”

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

28 ስለዚህ ምድር ታለቅሳለች፥ በላይም ሰማይ ይጠቁራል፤ ተናግሬአለሁና፥ አስቤአለሁም፤ አልጸጸትም ከእርሱም አልመለስም።”

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

28 ምድር ታለቅሳለች፤ ሰማይም በጨለማ ይጋረዳል፤ ይህን እግዚአብሔር ተናግሮአል፤ ሐሳቡም አይለወጥም፤ ቊርጥ ውሳኔ አድርጎአል፤ ወደ ኋላም አይመለስም።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

28 ስለዚህ ምድር ታለቅሳለች፥ በላይም ሰማይ ይጠቍራል፥ ተናግሬአለሁና፥ አስቤአለሁም፥ አልጸጸትም ከእርሱም አልመለስም።

See the chapter Copy




ኤርምያስ 4:28
34 Cross References  

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሰው የሚ​ታ​ለል አይ​ደ​ለም። እንደ ሰው ልጅም የሚ​ዛ​ት​በት አይ​ደ​ለም፤ እርሱ ያለ​ውን አያ​ደ​ር​ገ​ው​ምን? አይ​ና​ገ​ረ​ው​ምን? አይ​ፈ​ጽ​መ​ው​ምን?


ስለ​ዚህ ምድ​ሪቱ ታለ​ቅ​ሳ​ለች፤ በእ​ር​ስ​ዋም ከሚ​ቀ​መጡ ሁሉ ከም​ድር አራ​ዊ​ትና ከሰ​ማይ ወፎች፤ ከም​ድ​ርም ተን​ቀ​ሳ​ቃ​ሾች ጋር ትጠ​ፋ​ለች፤ የባ​ሕ​ሩም ዓሦች ያል​ቃሉ።


በሚ​ኖ​ሩ​ባት ሰዎች ክፋት ምድ​ሪቱ የም​ታ​ለ​ቅ​ሰ​ውና የዱሩ ሣርስ ሁሉ የሚ​ደ​ር​ቀው እስከ መቼ ነው? እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍጻ​ሜ​ያ​ች​ንን አያ​ይም ብለ​ዋ​ልና እን​ስ​ሶ​ችና ወፎ​ችም ጠፍ​ተ​ዋል።


ሰማ​ይን በጨ​ለማ እሸ​ፍ​ነ​ዋ​ለሁ፤ መጋ​ረ​ጃ​ው​ንም ማቅ አደ​ር​ጋ​ለሁ።”


በዚ​ያም ቀን እንደ ባሕር መት​መም ይተ​ም​ሙ​ባ​ቸ​ዋል፤ ወደ ምድ​ርም ይመ​ለ​ከ​ታሉ፤ ድቅ​ድቅ ጨለ​ማን ያያሉ፤ ይጨ​ነ​ቃ​ሉም።


ስድስተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ አየሁ፤ ታላቅም የምድር መናወጥ ሆነ፤ ፀሐይም እንደ ማቅ ጠጕር ጥቁር ሆነ፤ ጨረቃም በሞላው እንደ ደም ሆነ፤


በመ​ሐላ የሾ​መ​ውን ግን፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማለ፥ አይ​ጸ​ጸ​ት​ምም፤ አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት የዘ​ለ​ዓ​ለም ካህን ነህ” አለው።


እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚ​ሠራ እንደ እርሱ አሳብ አስ​ቀ​ድ​መን የተ​ወ​ሰን በእ​ርሱ ርስ​ትን ተቀ​በ​ልን።


እንደ ወደ​ደም በእ​ርሱ የወ​ሰ​ነ​ውን፥ የፈ​ቃ​ዱን ምሥ​ጢር ገለ​ጠ​ልን።


ቀትር በሆነ ጊዜም በስ​ድ​ስት ሰዓት ፀሐይ ጨለመ፤ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረ​ስም ዓለም ሁሉ ጨለማ ሆነ።


ስድስት ሰዓትም በሆነ ጊዜ፥ እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።


ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።


እር​ሻው ምድረ በዳ ሆኖ​አል፤ ምድ​ሪ​ቱም ታል​ቅስ፤ እህሉ ጠፍ​ቶ​አ​ልና፥ ወይ​ኑም ደር​ቆ​አ​ልና፥ ዘይ​ቱም ጐድ​ሎ​አ​ልና።


ከሲ​ኦል እጅ እታ​ደ​ጋ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ከሞ​ትም እቤ​ዣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ሞት ሆይ! መው​ጊ​ያህ ወዴት አለ? ሲኦል ሆይ! ድል መን​ሣ​ትህ ወዴት አለ? ደስ​ታህ ከዐ​ይ​ኖ​ችህ ተሰ​ወ​ረች።


እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተና​ግ​ሬ​አ​ለሁ፤ እመ​ጣ​ለሁ፤ እኔም አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ፤ አል​ተ​ውም፤ አል​ራ​ራም፤ አል​ጸ​ጸ​ትም፤ እንደ መን​ገ​ድ​ሽና እንደ ሥራ​ሽም እፈ​ር​ድ​ብ​ሻ​ለሁ፥ ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር። ስለ​ዚህ የሰ​ውን ደም እንደ አፈ​ሰ​ስሽ እኔ እፈ​ር​ድ​ብ​ሻ​ለሁ፤ እንደ ኀጢ​አ​ት​ሽም ተበ​ቅዬ አጠ​ፋ​ሻ​ለሁ፤ ስም​ሽም ጐሰ​ቈለ፥ ብዙ ኀዘ​ን​ንም ታዝ​ኛ​ለሽ።”


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጽኑ ቍጣ የል​ቡን አሳብ ሠርቶ እስ​ኪ​ፈ​ጽም ድረስ አይ​መ​ለ​ስም፤ በኋ​ለ​ኛ​ውም ዘመን ታው​ቁ​ታ​ላ​ችሁ።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍጣ የል​ቡን ዐሳብ ሠርቶ እስ​ኪ​ፈ​ጽም ድረስ አይ​መ​ለ​ስም፤ በኋ​ለ​ኛ​ውም ዘመን ያው​ቁ​ታል።


ዝሙ​ታ​ቸው ምድ​ርን ሞል​ት​ዋ​ልና፥ ከመ​ር​ገም ፊት የተ​ነሣ ምድር አል​ቅ​ሳ​ለች፤ የም​ድረ በዳ ማሰ​ሪ​ያው ሁሉ ደር​ቆ​አል፤ ሥራ​ቸ​ውና ድካ​ማ​ቸው ከንቱ ሆነ።


ይሁዳ አለ​ቀ​ሰች፤ ደጆ​ች​ዋም ባዶ ሆኑ፤ በም​ድ​ርም ላይ ጨለሙ፤ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ጩኸት ከፍ ከፍ ብሎ​አል።


እር​ስ​ዋም ለፍ​ጹም ጥፋት ሆና​ለች፤ ስለ እኔም ምድር ሁሉ ባድማ ሆና​ለች፤ በል​ቡም የሚ​ያ​ኖ​ራት የለም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለኝ፥ “ስለ​ዚህ ሕዝብ አንተ አት​ጸ​ልይ፤ ይቅር እላ​ቸው ዘንድ አት​ማ​ል​ደኝ፤ የእ​ነ​ር​ሱን ነገር አል​ሰ​ማ​ህ​ምና ትለ​ም​ን​ላ​ቸው ዘንድ ወደ እኔ አት​ምጣ።”


ሰማ​ያት እንደ መጽ​ሐፍ ጥቅ​ልል ይጠ​ቀ​ለ​ላሉ፤ ከወ​ይ​ንና ከበ​ለ​ስም ቅጠል እን​ደ​ሚ​ረ​ግፍ ከዋ​ክ​ብት ሁሉ ይረ​ግ​ፋሉ።


ምድ​ርም አለ​ቀ​ሰች፤ ጠፋ​ችም፤ ዓለም ተገ​ለ​በ​ጠች፤ የም​ድ​ርም ታላ​ላ​ቆች አለ​ቀሱ።


እስ​ራ​ኤል ለሁ​ለት ይከ​ፈ​ላል፤ ከእ​ን​ግ​ዲ​ህም አይ​ሰ​በ​ሰ​ብም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እንደ ሰው የሚ​ጸ​ጸት አይ​ደ​ለ​ምና አይ​ጸ​ጸ​ትም” አለው።


በባ​ቢ​ሎን ቅጥ​ሮች ላይ ዓላ​ማ​ውን አንሡ፤ ከጕ​ራ​ን​ጕ​ሬ​አ​ችሁ ጋር ጽኑ፤ ተመ​ል​ካ​ቾ​ችን አቁሙ፤ መሣ​ሪ​ያ​ች​ሁን አዘ​ጋጁ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በባ​ቢ​ሎን በሚ​ኖ​ሩት ላይ የተ​ና​ገ​ረ​ውን ያደ​ርግ ዘንድ ጀም​ሮ​አ​ልና።


ፌ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያሰ​በ​ውን አደ​ረገ፤ በቀ​ድሞ ዘመን ያዘ​ዘ​ው​ንም ቃል ፈጸመ፤ አፈ​ረ​ሳት፤ አል​ራ​ራ​ላ​ት​ምም፤ ጠላ​ት​ንም ደስ አሰ​ኘ​ብሽ፤ የጠ​ላ​ቶ​ች​ሽ​ንም ቀንድ ከፍ ከፍ አደ​ረገ።


የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ አባቶቻችሁ እጅግ ባስቈጡኝ ጊዜ ክፉ ለማድረግ እንዳሰብሁ፥ እንዳልተጸጸትሁም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥


Follow us:

Advertisements


Advertisements