Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




ኤርምያስ 36:2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

2 “አንድ የመ​ጽ​ሐፍ ክር​ታስ ውሰድ፥ ለአ​ን​ተም ከተ​ና​ገ​ር​ሁ​በት ቀን ከይ​ሁዳ ንጉሥ ከኢ​ዮ​ስ​ያስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልና በይ​ሁዳ ላይ በአ​ሕ​ዛ​ብም ሁሉ ላይ የተ​ና​ገ​ር​ሁ​ህን ቃል ሁሉ ጻፍ​በት።

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

2 “የብራና ጥቅልል ውሰድ፤ ለአንተም መናገር ከጀመርሁበት ከኢዮስያስ ዘመነ መንግሥት አንሥቶ እስካሁን ድረስ ስለ እስራኤል፣ ስለ ይሁዳና ስለ ሌሎች ሕዝቦች ሁሉ የነገርሁህን ቃል ሁሉ ጻፍበት፤

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

2 “አንድ የመጽሐፍ ክርታስ ውሰድ፥ ለአንተም ከተናገርሁበት ቀን፥ ከኢዮስያስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በእስራኤልና በይሁዳ ላይ፥ በአሕዛብም ሁሉ ላይ ለአንተ የተናገርሁትን ቃላት ሁሉ ጻፍበት።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

2 “እኔ እግዚአብሔር አንተን ማናገር ከጀመርኩበት ማለትም ኢዮስያስ ከነገሠበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ስለ እስራኤል፥ ስለ ይሁዳ ሕዝብና ስለ ሌሎችም ሕዝቦች ሁሉ የነገርኩህን ቃል ሁሉ በብራና ጻፈው፤

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

2 አንድ የመጽሐፍ ክርታስ ውሰድ፥ ለአንተም ከተናገርሁበት ቀን ከኢዮስያስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በእስራኤልና በይሁዳ ላይ በአሕዛብም ሁሉ ላይ የተናገርሁህን ቃል ሁሉ ጻፍበት።

See the chapter Copy




ኤርምያስ 36:2
34 Cross References  

“የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የነ​ገ​ር​ሁ​ህን ቃል ሁሉ በመ​ጽ​ሐፍ ጻፍ።


“ከይ​ሁዳ ንጉሥ ከአ​ሞጽ ልጅ ከኢ​ዮ​ስ​ያስ ከዐ​ሥራ ሦስ​ተ​ኛው ዓመት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ባሉት በእ​ነ​ዚህ በሃያ ሦስቱ ዓመ​ታት፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ወደ እኔ መጣ፤ እኔም ማልጄ ተነ​ሥቼ ተና​ገ​ር​ኋ​ችሁ፤ ነገር ግን አል​ሰ​ማ​ች​ሁ​ኝም።”


እነሆ ትነ​ቅ​ልና ታፈ​ርስ ዘንድ፥ ታጠ​ፋና ትገ​ለ​ብጥ ዘንድ፥ ትሠ​ራና ትተ​ክል ዘንድ በአ​ሕ​ዛ​ብና በመ​ን​ግ​ሥ​ታት ላይ ዛሬ ሾሜ​ሃ​ለሁ።”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን፥ “የዐ​ማ​ሌ​ቅን ዝክር ከሰ​ማይ በታች ጨርሼ እደ​መ​ስ​ሳ​ለ​ሁና ይህን ለመ​ታ​ሰ​ቢያ በመ​ጽ​ሐፍ ጻፈው፤ በኢ​ያ​ሱም ጆሮ ተና​ገር” አለው።


በአ​የ​ሁም ጊዜ፥ እነሆ እጅ ወደ እኔ ተዘ​ር​ግታ ነበር፤ እነ​ሆም የመ​ጽ​ሐፍ ጥቅ​ልል ነበ​ረ​ባት።


ሠራ​ያም የቤቱ አዛዥ ነበረ፤ በባ​ቢ​ሎ​ንም ላይ የሚ​መ​ጣ​ውን ክፉ ነገር ሁሉ፥ ስለ ባቢ​ሎን የተ​ጻ​ፈ​ውን ይህን ቃል ሁሉ ኤር​ም​ያስ በአ​ንድ መጽ​ሐፍ ላይ ጻፈው።


ይሁ​ዳም ሦስ​ትና አራት ዐምድ ያህል በአ​ነ​በበ ቍጥር፥ ንጉሡ በብ​ርዕ መቍ​ረጫ ቀደ​ደው፤ ክር​ታ​ሱ​ንም በም​ድጃ ውስጥ በአ​ለው እሳት ፈጽሞ እስ​ኪ​ቃ​ጠል ድረስ በም​ድጃ ውስጥ ወደ አለው እሳት ጣለው።


አንተ ግን ገብ​ተህ ከአፌ የጻ​ፍ​ኸ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል በጾም ቀን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በሕ​ዝቡ ጆሮ በክ​ር​ታሱ አን​ብብ፤ ደግ​ሞም ከከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው በሚ​ወጡ በይ​ሁዳ ሰዎች ሁሉ ጆሮ አን​ብ​በው።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለኝ፥ “ታላቅ አዲስ ሰሌዳ ወስ​ደህ፦ ‘ቸኩ​ለህ ማርክ፤ ፈጥ​ነ​ህም በዝ​ብዝ’ ብለህ በሰው ብርዕ ጻፍ​በት።


ጠላ​ቶ​ቼም ሁሉ ይጠ​ቃ​ቀ​ሱ​ብ​ኛል፥ በእኔ ላይም ክፋ​ትን ይመ​ክ​ራሉ።


በሜ​ዶን አው​ራጃ ባለው ባሪ በሚ​ባል ከተማ በን​ጉሡ ቤት ውስጥ አንድ ጥቅ​ልል ተገኘ፤ በው​ስ​ጡም ይህ ነገር ለመ​ታ​ሰ​ቢያ ተጽፎ ነበር።


ብዙ ሕጎ​ችን እጽ​ፍ​ለ​ታ​ለሁ፤ ነገር ግን ሥር​ዐ​ቱና የተ​ወ​ደ​ደው መሠ​ዊ​ያው እንደ እን​ግዳ ነገር ተቈ​ጠሩ።


በይ​ሁዳ ንጉሥ በኢ​ዮ​ስ​ያስ ልጅ በኢ​ዮ​አ​ቄም በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥት እነ​ዚ​ህን ቃላት ከኤ​ር​ም​ያስ አፍ በመ​ጽ​ሐፍ በጻ​ፋ​ቸው ጊዜ፥ ነቢዩ ኤር​ም​ያስ ለኔ​ርዩ ልጅ ለባ​ሮክ የተ​ና​ገ​ረው ቃል ይህ ነው።


የይ​ሁ​ዳ​ንም ንጉሥ ኢዮ​አ​ቄ​ምን እን​ዲህ በለው፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ አንተ፦ የባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በር​ግጥ ይመ​ጣል፤ ይች​ንም ሀገር ያፈ​ር​ሳ​ታል፤ ሰውና እን​ስ​ሳም ያል​ቃሉ ብለህ ለምን ጻፍ​ህ​በት? ብለህ ይህን ክር​ታስ አቃ​ጥ​ለ​ሃል።


የያ​ዕ​ቆብ ቤት የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ቤት ወገ​ኖች ሁሉ ሆይ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስሙ።


“በእ​ና​ትህ ሆድ ሳል​ሠ​ራህ አው​ቄ​ሃ​ለሁ፤ ከማ​ኅ​ፀ​ንም ሳት​ወጣ ቀድ​ሼ​ሃ​ለሁ፥ ለአ​ሕ​ዛ​ብም ነቢይ አድ​ር​ጌ​ሃ​ለሁ።”


የሚ​ያ​ደ​ም​ጠ​ኝን ማን በሰ​ጠኝ! የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም እጅ አል​ፈ​ራሁ እንደ ሆነ፥ የሚ​ያ​ስ​ፈ​ር​ድ​ብኝ የክስ ጽሑፍ ምነው በኖ​ረኝ!


እን​ዲ​ህም ሆነ፤ ሙሴ የዚ​ህን ሕግ ቃሎች እስከ መጨ​ረሻ በመ​ጽ​ሐፍ ጽፎ ከፈ​ጸመ በኋላ፥


ያን​ጊዜ እነሆ፥ በመ​ጽ​ሐፍ ራስ ስለ እኔ እንደ ተጻፈ፥ አም​ላኬ ሆይ፥ ፈቃ​ድ​ህን አደ​ርግ ዘንድ መጥ​ቻ​ለሁ አልሁ።”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እጁን ዘር​ግቶ አፌን ዳሰሰ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለኝ፥ “እነሆ፥ ቃሌን በአ​ፍህ ውስጥ አኑ​ሬ​አ​ለሁ፤


አለ​ቆ​ቹም ሁሉ፥ “በሕ​ዝቡ ጆሮ ያነ​በ​ብ​ኸ​ውን ክር​ታስ በእ​ጅህ ይዘህ ና” ብለው የኩሲ ልጅ የሰ​ሌ​ምያ ልጅ የና​ታ​ንያ ልጅ ይሁ​ዳን ወደ ኔርዩ ልጅ ወደ ባሮክ ላኩ። የኔ​ር​ዩም ልጅ ባሮክ ክር​ታ​ሱን በእጁ ይዞ ወደ እነ​ርሱ ወረደ።


ባሮ​ክም፥ “ኤር​ም​ያስ ይህን ቃል ከአፉ ይነ​ግ​ረኝ ነበር፤ እኔም በመ​ጽ​ሐፉ ላይ እጽፍ ነበር” ብሎ መለ​ሰ​ላ​ቸው።


Follow us:

Advertisements


Advertisements