Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




ኤርምያስ 2:24 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

24 በም​ድረ በዳ ባሉ ውኃ​ዎች ተዘ​ረ​ጋች፤ በሰ​ው​ነ​ቷም ምኞት ትወ​ሰ​ዳ​ለች፤ ይይ​ዟ​ታል፤ የሚ​መ​ል​ሳት ግን የለም፤ የሚ​ሹ​አ​ትም አይ​ደ​ክ​ሙም፤ በተ​ዋ​ረ​ደ​ች​በ​ትም ጊዜ ያገ​ኙ​አ​ታል።

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

24 በምድረ በዳ እንደ ለመደች፣ በፍትወቷ ነፋስን እንደምታነፈንፍ፣ የሜዳ አህያ ነሽ፤ ከመጐምጀቷ ማን ሊገታት ይችላል? ለሚፈልጓት ሁሉ ያለ ምንም ድካም በፍትወቷ ወራት በቀላሉ ትገኝላቸዋለች።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

24 በምኞትዋ ነፋስን እንደምታሸትት፥ በምድረ በዳ እንደ ለመደች እንደ ሜዳ አህያ ነሽ፤ ከጋለው ምኞትዋ የሚመልሳት ማን ነው? የሚሹአት ሁሉ አይደክሙም፥ በወራትዋ ያገኙአታል።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

24 በበረሓ መኖርን የለመደች የሜዳ አህያ፥ ፍትወት በተቀሰቀሰባት ጊዜ ማን ሊቈጣጠራት ይችላል? ወንዶች የሜዳ አህዮች ያሉበትን ስፍራ፥ ራስዋ አነፍንፋ ስለምትደርስበት፥ እነርሱ እርስዋን በመፈለግ መድከም አያስፈልጋቸውም።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

24 በምኞትዋ ነፋስን እንደምታሸትት፥ በምድረ በዳ እንደ ለመደች እንደ ሜዳ አህያ ነሽ፥ ከምኞትዋ የሚመልሳት ማን ነው? የሚሹአት ሁሉ አይደክሙም፥ በወራትዋ ያገኙአታል።

See the chapter Copy




ኤርምያስ 2:24
8 Cross References  

የሜዳ አህ​ዮ​ችም በወና ኮረ​ብታ ላይ ቆመ​ዋል፤ እንደ ሰገ​ኖም ወደ ነፋስ አለ​ከ​ለኩ፤ ሣርም የለ​ምና ዐይ​ኖ​ቻ​ቸው ጠወ​ለጉ።


እስ​ኪ​ጠፉ ድረስ፥ ፊቴ​ንም እስ​ኪሹ ድረስ እሄ​ዳ​ለሁ፤ ወደ ስፍ​ራ​ዬም እመ​ለ​ሳ​ለሁ።


ግን​ዱን፥ “አንተ አባቴ ነህ፤ ድን​ጋ​ዩ​ንም፦ አንተ ወለ​ድ​ኸኝ” ይላሉ፤ ፊታ​ቸ​ው​ንም ሳይ​ሆን ጀር​ባ​ቸ​ውን ሰጡኝ፤ በመ​ከ​ራ​ቸው ጊዜ ግን፥ “ተነ​ሥ​ተህ አድ​ነን ይላሉ።


ነገር ግን በከ​ንቱ ነገ​ርን የሚ​ፈ​ልግ ሰው፥ ከሴ​ትም የሚ​ወ​ለድ ሟች የሜዳ አህ​ያን ይመ​ስ​ላል።


ለብ​ቻ​ውም እን​ደ​ሚ​ቀ​መጥ እንደ ምድረ በዳ አህያ ወደ አሦር ወጥ​ተ​ዋል፤ ኤፍ​ሬ​ምም እንደ ገና ለመ​ለመ፤ እጅ መን​ሻ​ንም ወደደ።


እር​ስዋ የም​ት​ወ​ል​ድ​በ​ት​ንስ ሙሉ ወራት ትቈ​ጥ​ራ​ለ​ህን? ከም​ጥስ ትገ​ላ​ግ​ላ​ታ​ለ​ህን?


ለአ​መ​ን​ዝ​ራ​ዎች ሁሉ ዋጋ ይሰ​ጡ​አ​ቸ​ዋል፤ አንቺ ግን ለወ​ዳ​ጆ​ችሽ ሁሉ ዋጋ ትሰ​ጫ​ለሽ፤ ከአ​ን​ቺም ጋር ለማ​መ​ን​ዘር በዙ​ሪ​ያሽ ይገ​ቡ​ብሽ ዘንድ መማ​ለ​ጃን ትሰ​ጫ​ቸ​ዋ​ለሽ።


Follow us:

Advertisements


Advertisements