Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




ሆሴዕ 2:5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

5 እና​ታ​ቸው አመ​ን​ዝ​ራ​ለ​ችና፤ የወ​ለ​ደ​ቻ​ቸ​ውም፥ “እን​ጀ​ራ​ዬ​ንና ውኃ​ዬን፥ ቀሚ​ሴ​ንና መደ​ረ​ቢ​ያ​ዬን፥ ዘይ​ቴ​ንና የሚ​ገ​ባ​ኝን ሁሉ የሚ​ሰ​ጡኝ ወዳ​ጆ​ችን እከ​ተ​ላ​ቸው ዘንድ እሄ​ዳ​ለሁ” ብላ​ለ​ችና አሳ​ፈ​ረ​ቻ​ቸው።

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

5 እናታቸው አመንዝራ ናት፤ በውርደትም ፀንሳቸዋለች፤ እርሷም፣ ‘እንጀራዬንና ውሃዬን ይሰጡኛል፤ ሱፌንና የሐር ልብሴን፣ ዘይቴንና መጠጤን ይሰጡኛል፤ ስለዚህ ውሽሞቼን ተከትዬ እሄዳለሁ’ አለች።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

5 አለበለዚያ ዕራቁትዋን እንድትሆን እገፍፋታለሁ፥ እንደ ተወለደችበትም ቀን አደርጋታለሁ፥ እንደ ምድረ በዳና እንደ ደረቅ ምድር አደርጋታለሁ፥ በጥምም እገድላታለሁ።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

5 እናታቸው አመንዝራ ስለ ሆነች እነርሱን ባሳፋሪ መንገድ ፀንሳቸዋለች፤ እርስዋም ይህን ያደረገችው ምግቤንና ውሃዬን፥ የሱፍና የተልባ እግር ልብሴን፥ ዘይቴንና መጠጤን የሚሰጡኝ ስለ ሆነ ፍቅረኞቼን ተከትዬ እሄዳለሁ ብላ ነው።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

5 ዕራቁትዋን እንዳልገፍፋት፥ እንደ ተወለደችበትም ቀን እንዳላደርጋት፥ እንደ ምድረ በዳና እንደ ደረቅ ምድር እንዳላደርጋት፥

See the chapter Copy




ሆሴዕ 2:5
33 Cross References  

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ወደ ሌሎች አማ​ል​ክት ቢመ​ለ​ሱና የዘ​ቢብ ጥፍ​ጥ​ፍን ቢወ​ድዱ እን​ኳን፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ደ​ሚ​ወ​ድ​ዳ​ቸው አን​ተም ክፋ​ትና ዝሙት ያለ​ባ​ትን ሴት ውደድ” አለኝ።


እር​ስ​ዋም እህ​ል​ንና ወይ​ንን ዘይ​ት​ንም የሰ​ጠ​ኋት፥ ብር​ንና ወር​ቅን ያበ​ዛ​ሁ​ላት እኔ እንደ ሆንሁ አላ​ወ​ቀ​ችም። እር​ስዋ ግን ወር​ቁ​ንና ብሩን ለጣ​ዖት አደ​ረ​ገች።


ፍርድ መል​ቶ​ባት የነ​በረ የታ​መ​ነ​ች​ይቱ የጽ​ዮን ከተማ እን​ዴት ጋለ​ሞታ ሆነች! ጽድቅ አድ​ሮ​ባት ነበር፤ አሁን ግን ወን​በ​ዴ​ዎ​ችና ነፍሰ ገዳ​ዮች አሉ​ባት።


እስ​ራ​ኤ​ልን በም​ድረ በዳ እንደ አለ ወይን ሆኖ አገ​ኘ​ሁት፤ አባ​ቶ​ቻ​ች​ሁ​ንም በመ​ጀ​መ​ሪ​ያዋ ዓመት እንደ በለስ በኵ​ራት ሆነው አየ​ኋ​ቸው፤ እነ​ርሱ ግን ወደ ብዔ​ል​ፌ​ጎር መጡ፤ ለነ​ው​ርም ተለዩ፤ እንደ ወደ​ዱ​ትም ርኩስ ሆኑ።


ለብ​ቻ​ውም እን​ደ​ሚ​ቀ​መጥ እንደ ምድረ በዳ አህያ ወደ አሦር ወጥ​ተ​ዋል፤ ኤፍ​ሬ​ምም እንደ ገና ለመ​ለመ፤ እጅ መን​ሻ​ንም ወደደ።


በቀ​ንም ትደ​ክ​ማ​ለህ፤ ነቢ​ዩም ከአ​ንተ ጋር ይደ​ክ​ማል፤ እና​ታ​ች​ሁም ሌሊ​ትን ትመ​ስ​ላ​ለች።


እና​ታ​ችሁ ሚስቴ አይ​ደ​ለ​ች​ምና፥ እኔም ባልዋ አይ​ደ​ለ​ሁ​ምና እና​ታ​ች​ሁን ተዋ​ቀ​ሱ​አት። ዝሙ​ቷን ከፊቷ፥ ምን​ዝ​ር​ና​ዋ​ንም ከጡ​ቶ​ችዋ መካ​ከል አስ​ወ​ግ​ዳ​ለሁ።


ይሁዳ ሆይ! አማ​ል​ክ​ትህ እንደ ከተ​ሞ​ችህ ቍጥር እን​ዲሁ ናቸው፤ እንደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም መን​ገ​ዶች ቍጥር ለነ​ው​ረኛ ነገር ለበ​ዓል ታጥ​ኑ​ባ​ቸው ዘንድ መሠ​ዊ​ያ​ዎ​ችን አድ​ር​ጋ​ች​ኋል።


ከጥ​ንት ጀምሬ ቀን​በ​ር​ሽን ሰብ​ሬ​አ​ለሁ፤ እስ​ራ​ት​ሽ​ንም ቈር​ጫ​ለሁ፤ አን​ቺም፦ አላ​ገ​ለ​ግ​ልም አልሽ፤ ነገር ግን ከፍ ባለው ኮረ​ብታ ሁሉ ላይ፤ ከለ​ም​ለ​ምም ዛፍ ሁሉ በታች ለማ​መ​ን​ዘር ተጋ​ደ​ምሽ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “እና​ታ​ች​ሁን የፈ​ታ​ሁ​በት የፍ​ችዋ ደብ​ዳቤ የት አለ? ወይስ እና​ን​ተን የሸ​ጥሁ ከአ​በ​ዳ​ሪ​ዎች ለማን ነው? እነሆ፥ ስለ ኀጢ​አ​ታ​ችሁ ተሸ​ጣ​ች​ኋል፤ ስለ በደ​ላ​ች​ሁም እና​ታ​ችሁ ተፈ​ት​ታ​ለች።


የፍ​ል​ስ​ጥ​ኤም መሳ​ፍ​ን​ትም፥ “አም​ላ​ካ​ችን ጠላ​ታ​ች​ንን ሶም​ሶ​ንን በእ​ጃ​ችን አሳ​ልፎ ሰጠን” እያሉ ለአ​ም​ላ​ካ​ቸው ለዳ​ጎን ታላቅ መሥ​ዋ​ዕት ይሠዉ ዘንድ፥ ደስም ይላ​ቸው ዘንድ ተሰ​በ​ሰቡ።


ወደ ሆሴዕ የመጣ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የቃሉ መጀ​መ​ሪያ ይህ ነው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆሴ​ዕን፥ “ምድ​ሪቱ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ርቃ ታመ​ነ​ዝ​ራ​ለ​ችና ሂድ፤ ዘማ​ዊ​ቱን ሴትና የዘ​ማ​ዊ​ቱን ልጆች ለአ​ንተ ውሰድ” አለው።


ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሆይ፤ ነፍሴ ከአ​ንቺ እን​ዳ​ት​ለይ፥ አን​ቺ​ንም ባድ​ማና ወና እን​ዳ​ላ​ደ​ር​ግሽ፥ ተግ​ሣ​ጽን ተቀ​በዪ።


በል​ብ​ሽም፦ እን​ዲህ ያለ ነገር ስለ ምን ደረ​ሰ​ብኝ? ብትዪ፥ ከኀ​ጢ​አ​ትሽ ብዛት የተ​ነሣ ልብ​ስሽ በስ​ተ​ኋ​ላሽ ተገ​ፎ​አል፤ ተረ​ከ​ዝ​ሽም ተገ​ል​ጦ​አል።


በተ​ወ​ለ​ድሽ ጊዜ በዚ​ያው ቀን እት​ብ​ትሽ አል​ታ​ተ​በም፤ ንጹ​ሕም ትሆኚ ዘንድ በውኃ አል​ታ​ጠ​ብ​ሽም፤ በጨ​ውም አል​ተ​ወ​ለ​ወ​ል​ሽም፤ በጨ​ር​ቅም አል​ተ​ጠ​ቀ​ለ​ል​ሽም፤ በጭ​ንም አል​ታ​ቀ​ፍ​ሽም።


“ስለ​ዚህ ዘማ ሆይ! የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስሚ።


በእ​ጃ​ቸ​ውም አሳ​ልፌ እሰ​ጥ​ሻ​ለሁ፤ የም​ን​ዝ​ር​ና​ሽ​ንም ስፍራ ያፈ​ር​ሳሉ፤ ከፍ ያለ​ው​ንም ቦታ​ሽን ይገ​ለ​ብ​ጣሉ፤ ልብ​ስ​ሽ​ንም ይገ​ፉ​ሻል፤ የክ​ብ​ር​ሽ​ንም ጌጥ ይወ​ስ​ዳሉ፤ ዕራ​ቁ​ት​ሽ​ንም ይተ​ዉ​ሻል፤ ቷረ​ጃ​ለ​ሽም።


በዚያ ቀን መልከ መል​ካ​ሞቹ ደና​ግ​ልና ጐበ​ዛ​ዝቱ በጥም ይዝ​ላሉ።


Follow us:

Advertisements


Advertisements