Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




ዘፍጥረት 43:18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

18 እነ​ዚ​ያም ሰዎች ወደ ዮሴፍ ቤት እንደ ገቡ በአዩ ጊዜ እን​ዲህ አሉ፥ “በዓ​ይ​በ​ታ​ችን ቀድሞ ስለ ተመ​ለ​ሰው ብር ሊተ​ነ​ኰ​ሉ​ብን፥ ሊወ​ድ​ቁ​ብ​ንም፥ እኛ​ንም በባ​ር​ነት ሊገ​ዙን፥ አህ​ዮ​ቻ​ች​ን​ንም ሊወ​ስዱ ወደ​ዚህ አስ​ገ​ቡን።”

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

18 ሰዎቹም ወደ ዮሴፍ ቤት በመወሰዳቸው ፈሩ፤ እነርሱም፣ “ወደዚህ የመጣነው፣ ቀደም ሲል እዚህ መጥተን ስንመለስ በየስልቾቻችን ውስጥ ተመልሶ በተጨመረው ብር ሰበብ ነው። ሰውየው ጥቃት ሊፈጽምብን፣ አስገድዶ ባሮቹ ሊያደርገንና አህዮቻችንን ሊቀማን ይፈልጋል” ብለው ሠጉ።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

18 የእስራኤልም ልጆች ወደ ዮሴፍ ቤት በመወሰዳቸው ፈሩ፤ እነርሱም፥ “ወደዚህ የመጣነው፥ ቀደም ሲል እዚህ መጥተን ስንመለስ በየስልቾቻችን ውስጥ ተመልሶ በተጨመረው ብር ሰበብ ነው። ሰውዬው ጥቃት ሊፈጽምብን፥ አስገድዶ ባሮቹ ሊያደርገንና አህዮቻችንን ሊቀማን ይፈልጋል” ብለው ሠጉ።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

18 “ወደ እዚህ ያመጡን በመጀመሪያ ጊዜ በስልቻዎቻችን ውስጥ ተመልሶ ስለ ተገኘው ገንዘብ ሳይሆን አይቀርም” በማለት፤ ሰዎቹ ወደ ዮሴፍ ቤት በሚሄዱበት ጊዜ እጅግ ፈሩ፤ “በዚህ ምክንያት ያሠቃዩናል፤ አህዮቻችንን ወስደው እኛንም የእነርሱ ባሪያዎች ያደርጉናል” ብለውም አሰቡ።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

18 እነርሱም ወደ ዮሴፍ ቤት ስለ ገቡ ፈሩ እንዲህም አሉ፦ በዓይበታችን ቀድሞ ስለ ተመለሰው ብር ሊተነኮልብን ሊወድቅብንም እኛንም በባርነት ሊገዛ አህዮቻችንንም ሊወስድ ወደዚህ አስገባን።

See the chapter Copy




ዘፍጥረት 43:18
20 Cross References  

እን​ዲ​ህም ሆነ፤ ዓይ​በ​ታ​ቸ​ውን በፈቱ ጊዜ እነሆ፥ ከእ​ነ​ርሱ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸው ብራ​ቸ​ውን በዓ​ይ​በ​ታ​ቸው ተቋ​ጥሮ አገ​ኙት፤ እነ​ር​ሱም አባ​ታ​ቸ​ውም የተ​ቋ​ጠረ ብራ​ቸ​ውን አይ​ተው ፈሩ።


ያችም ትእ​ዛዝ ለኀ​ጢ​አት ምክ​ን​ያት ሆነ​ቻት፤ ምኞ​ት​ንም ሁሉ አመ​ጣ​ች​ብኝ፤ ቀድሞ ግን ኦሪት ሳት​ሠራ ኀጢ​አት ሙት ነበ​ረች።


ሄሮድስ ግን ሰምቶ “እኔ ራሱን ያስቈረጥሁት ዮሐንስ ይህ ነው፤ እርሱ ከሙታን ተነሥቶአል፤” አለ።


ለዳ​ዊት ቤትም፥ “አራም ከኤ​ፍ​ሬም ጋር ተባ​ብ​ረ​ዋል” የሚል ወሬ ተነ​ገረ፤ የእ​ር​ሱም ልብ የሕ​ዝ​ቡም ልብ የዱር ዛፍ በነ​ፋስ እን​ደ​ሚ​ና​ወጥ ተና​ወጠ።


ቀኑ የአ​ንተ ነው፥ ሌሊ​ቱም የአ​ንተ ነው፤ አንተ ፀሐ​ይ​ንና ጨረ​ቃን ፈጠ​ርህ።


ክፋ​ትን ወደ ጠላ​ቶች ይመ​ል​ሳ​ታል፤ በእ​ው​ነ​ት​ህም አጥ​ፋ​ቸው።


እንደ ወደደ አደ​ረ​ገ​ብኝ፤ በመ​ከ​ራም እዛ​ብ​ራ​ለሁ።


የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግጥ ድም​ፅም በጆ​ሮው ነው፤ በደ​ኅ​ን​ነ​ትም ይኖር ዘንድ ተስፋ በሚ​ያ​ደ​ር​ግ​በት ጊዜ ጥፋት ይመ​ጣ​በ​ታል።


አባ​ቱና እና​ቱም ነገሩ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆነ አላ​ወ​ቁም፤ እርሱ ከፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን በቀ​ልን ይመ​ልስ ዘንድ ይፈ​ልግ ነበ​ርና። በዚ​ያም ወራት ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን እስ​ራ​ኤ​ልን ይገዙ ነበር።


ማኑ​ሄም ሚስ​ቱን፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አይ​ተ​ና​ልና ሞትን እን​ሞ​ታ​ለን” አላት።


እነ​ሆም፦ በል​ጅህ ድን​ግ​ልና አላ​ገ​ኘ​ሁ​ባ​ትም ብሎ የነ​ውር ነገር አወ​ራ​ባት፤ የል​ጄም የድ​ን​ግ​ል​ናዋ ልብስ ይኸው ይላ​ቸ​ዋል። በከ​ተ​ማም ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ፊት ልብ​ሱን ይዘ​ረ​ጋሉ።


የነ​ውር ነገ​ርም ቢያ​መ​ጣ​ባት፥ እኔ ይህ​ችን ሴት ሚስቴ አድ​ርጌ አገ​ባ​ኋት፤ በደ​ረ​ስ​ሁ​ባ​ትም ጊዜ ድን​ግ​ል​ና​ዋን አላ​ገ​ኘ​ሁ​ባ​ትም ብሎ ክፉ ስም ቢያ​ወ​ጣ​ባት፥


ለወ​ን​ድ​ሞ​ቹም፥ “ብሬ ተመ​ለ​ሰ​ች​ልኝ፤ እር​ስ​ዋም በዓ​ይ​በቴ አፍ እነ​ኋት” አላ​ቸው። ልባ​ቸ​ውም ደነ​ገጠ፤ እየ​ታ​ወ​ኩም እርስ በር​ሳ​ቸው ተባ​ባሉ፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያደ​ረ​ገ​ብን ይህ ምን​ድን ነው?”


እነ​ር​ሱም እርስ በር​ሳ​ቸው እን​ዲህ ተባ​ባሉ፥ “በእ​ው​ነት ወን​ድ​ማ​ች​ንን በድ​ለ​ናል፤ እኛን በመ​ማ​ጠን ነፍሱ ስት​ጨ​ነቅ አይ​ተን አል​ሰ​ማ​ነ​ው​ምና፤ ስለ​ዚህ ይህ መከራ መጣ​ብን።”


ያም ሰው ዮሴፍ እን​ዳ​ለው አደ​ረገ፤ ሰዎ​ቹ​ንም ወደ ዮሴፍ ቤት አስ​ገባ።


ወደ ዮሴፍ ቤት አዛ​ዥም ቀረቡ፤ በቤ​ቱም ደጅ ተና​ገ​ሩት፤


ከእ​ነ​ር​ሱም አንዱ በአ​ደ​ሩ​በት ስፍራ ለአ​ህ​ዮቹ ገፈ​ራን ይሰጥ ዘንድ ዓይ​በ​ቱን ፈታ፤ ብሩ​ንም በዓ​ይ​በቱ አፍ ተቋ​ጥሮ አገኘ።


በየ​ዓ​ይ​በ​ታ​ችን አፍ ያገ​ኘ​ነ​ውን ብር እን​ኳን ይዘን ከከ​ነ​ዓን ሀገር ወደ አንተ ተመ​ል​ሰ​ናል፤ ከጌ​ታ​ህስ ቤት ወርቅ ወይስ ብር እን​ዴት እን​ሰ​ር​ቃ​ለን?


Follow us:

Advertisements


Advertisements