Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




1 ሳሙኤል 25:18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

18 አቤ​ግ​ያም ፈጥና፦ ሁለት መቶ እን​ጀራ፥ ሁለት አቁ​ማዳ የወ​ይን ጠጅ፥ አም​ስት የተ​ዘ​ጋጁ በጎች፥ አም​ስ​ትም መስ​ፈ​ሪያ በሶ፥ አንድ ጎሞር ዘቢብ፥ ሁለት መቶም የበ​ለስ ጥፍ​ጥፍ ወሰ​ደች፥ በአ​ህ​ዮ​ችም ላይ አስ​ጫ​ነች።

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

18 አቢግያም ጊዜ አላጠፋችም፤ ሁለት መቶ እንጀራ፣ ሁለት አቍማዳ የወይን ጠጅ፣ ዐምስት የተሰናዱ በጎች፣ ዐምስት መስፈሪያ የተጠበሰጠ እሸት፣ መቶ የወይን ዘለላና ዘቢብ፣ ሁለት መቶ ጥፍጥፍ የበለስ ፍሬ ወስዳ በአህዮች ላይ ጫነች።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

18 አቢጌልም ጊዜ አላጠፋችም፤ ሁለት መቶ እንጀራ፥ ሁለት አቁማዳ የወይን ጠጅ፥ አምስት የተሰናዱ በጎች፥ አምስት መስፈሪያ የተጠበሰ እሸት፥ መቶ የወይን ዘለላና ዘቢብ፥ ሁለት መቶ ጥፍጥፍ የበለስ ፍሬ ወስዳ በአህዮች ላይ ጫነች።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

18 አቢጌልም በፍጥነት ሁለት መቶ እንጀራ፥ ወይን ጠጅ የተሞላበት ሁለት የወይን አቁማዳ፥ አምስት የተጠበሱ በጎች፥ ዐሥራ ሰባት ኪሎ የተጠበሰ እሸት፥ አንድ መቶ ዘለላ ወይንና ሁለት መቶ የበለስ ፍሬ ጥፍጥፍ በአንድነት ሰብስባ በአህዮች ላይ ጫነች።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

18 አቢግያም ፈጥና ሁለት መቶ እንጀራ፥ ሁለት አቁማዳ የወይን ጠጅ፥ አምስትም የተዘጋጁ በጎች፥ አምስትም መስፈሪያ ጥብስ እሸት፥ አንድ መቶ ዘለላ ዘቢብ፥ ሁለት መቶም የበለስ ጥፍጥፍ ወሰደች፥ በአህዮችም ላይ አስጫነች።

See the chapter Copy




1 ሳሙኤል 25:18
14 Cross References  

ዳዊ​ትም ከተ​ራ​ራው ራስ ጥቂት እልፍ አለ። እነ​ሆም፥ የሜ​ም​ፌ​ቡ​ስቴ አገ​ል​ጋይ ሲባ ሁለት መቶ እን​ጀራ፥ አንድ መቶም ዘለላ ዘቢብ፥ አንድ መቶም ተምር፥ አንድ አቁ​ማ​ዳም ወይን ጠጅ የተ​ጫኑ ሁለት አህ​ዮች እየ​ነዳ ተገ​ና​ኘው።


አብረኸው በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ ጋር ፈጥነህ ተስማማ፤ ባላጋራ ለዳኛ እንዳይሰጥህ ዳኛም ለሎሌው፤ወደ ወህኒም ትጣላለህ፤


ሀብት ሰውን ከፍ ከፍ ያደርጋል፥ ከመኳንንት ጋርም ያኖረዋል።


በስውር ያለ ስጦታ ቍጣን ይመልሳል፥ ስጦታን የሚሸልግ ግን ጽኑ ቍጣን ያስነሣል።


ደግ​ሞም በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ደስታ ሆኖ​አ​ልና እስከ ይሳ​ኮ​ርና እስከ ዛብ​ሎን እስከ ንፍ​ታ​ሌ​ምም ድረስ ለእ​ርሱ አቅ​ራ​ቢያ የነ​በሩ በአ​ህ​ያና በግ​መል በበ​ቅ​ሎና በበሬ ላይ እን​ጀ​ራና ዱቄት የበ​ለስ ጥፍ​ጥ​ፍና የዘ​ቢብ ዘለላ የወ​ይ​ንም ጠጅ፥ ዘይ​ትም በሬ​ዎ​ች​ንና በጎ​ች​ንም፥ ፍየ​ሎ​ች​ንም በብዙ አድ​ር​ገው ያመጡ ነበር።


ነገር ግን ክፉ እን​ዳ​ላ​ደ​ር​ግ​ብሽ የከ​ለ​ከ​ለኝ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! እኔን ለመ​ገ​ና​ኘት ፈጥ​ነሽ ባል​መ​ጣሽ ኖሮ፥ እስ​ኪ​ነጋ ድረስ ለና​ባል አጥር ተጠ​ግቶ የሚ​ሸን አንድ ስንኳ ባል​ቀ​ረ​ውም ብዬ ነበር።”


እሴ​ይም ልጁን ዳዊ​ትን እን​ዲህ አለው፥ “ከዚህ በሶ አንድ የኢፍ መስ​ፈ​ሪያ እነ​ዚ​ህ​ንም ዐሥር እን​ጀ​ራ​ዎች ለወ​ን​ድ​ሞ​ችህ ውሰድ፤ ወደ ሰፈ​ሩም ፈጥ​ነህ ሂድና ለወ​ን​ድ​ሞ​ችህ ስጣ​ቸው፤


ስለ​ዚ​ህም በጌ​ታ​ች​ንና በቤቱ ሁላ ክፉ ነገር እን​ዲ​መጣ ተቈ​ር​ጦ​አ​ልና፥ እርሱ ክፉ ሰው ስለ ሆነ ማንም ሊና​ገ​ረው አይ​ች​ል​ምና የም​ታ​ደ​ር​ጊ​ውን ተመ​ል​ከ​ቺና ዕወቂ።”


Follow us:

Advertisements


Advertisements