Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




2 ዜና መዋዕል 27:5 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

5 ከአሞንም ልጆች ንጉሥ ጋር ተዋጋ አሸነፋአቸውም። በዚያም ዓመት የአሞን ልጆች መቶ መክሊት ብር፥ ዐሥር ሺህም የቆሬስ መስፈሪያ ስንዴ፥ ዐሥር ሺህም የቆሬስ መስፈሪያ ገብስ ሰጡት። እንዲሁም ደግሞ የአሞን ልጆች በሁለተኛውና በሦስተኛው ዓመት ተመሳሳ መጠን ያለውን ግብር ገበሩለት።

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

5 ኢዮአታም የአሞናውያንን ንጉሥ ወግቶ ድል አደረጋቸው። በዚያ ዓመትም አሞናውያን አንድ መቶ መክሊት ጥሬ ብር፣ ዐሥር ሺሕ ቆሮስ ስንዴና ዐሥር ሺሕ ቆሮስ ገብስ ገበሩለት። አሞናውያን በሁለተኛውና በሦስተኛው ዓመት ይህንኑ ግብር አመጡለት።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

5 በዐሞን ንጉሥና በሠራዊቱ ላይ ጦርነት ከፍቶ ድል አድርጎአቸው ነበር፤ ዐሞናውያንንም በየዓመቱ ለሦስት ዓመት በተከታታይ ሦስት ሺህ አራት መቶ ኪሎ የሚመዝን ብር፥ አንድ ሚሊዮን ኪሎ የሚመዝን ስንዴና እንዲሁም አንድ ሚሊዮን ኪሎ የሚመዝን ገብስ እንዲገብሩለት አስገደዳቸው።

See the chapter Copy

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

5 ከአ​ሞ​ንም ልጆች ንጉሥ ጋር ተዋጋ፤ አሸ​ነ​ፋ​ቸ​ውም። በዚ​ያም ዓመት የአ​ሞን ልጆች መቶ መክ​ሊት ብር፥ ዐሥር ሺህም የቆ​ሮስ መስ​ፈ​ሪያ ስንዴ፥ ዐሥር ሺህም የቆ​ሮስ መስ​ፈ​ሪያ ገብስ ግብር ሰጡት። እን​ዲ​ሁም ደግሞ የአ​ሞን ልጆ​ችና ንጉ​ሣ​ቸው በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው፥ በሁ​ለ​ተ​ኛ​ውና በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ሰጡት።

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

5 ከአሞንም ልጆች ንጉሥ ጋር ተዋጋ፤ አሸነፋአቸውም። በዚያም ዓመት የአሞን ልጆች መቶ መክሊት ብር፥ አሥር ሺህም የቆሬስ መስፈሪያ ስንዴ፥ አሥር ሺህም የቆሬስ መስፈሪያ ገብስ ሰጡት። እንዲሁም ደግሞ የአሞን ልጆች በሁለተኛውና በሦስተኛው ዓመት ሰጡት።

See the chapter Copy




2 ዜና መዋዕል 27:5
7 Cross References  

እንዲህም ሆነ፤ ከዚህ በኋላ የሞዓብና የአሞን ልጆች ከእነርሱም ጋር ምዑናውያን ኢዮሣፍጥን ሊወጉ መጡ።


በተራራማውም በይሁዳ አገር ላይ ከተሞችን ሠራ፥ በዱር ስፍራዎችም አምባዎችንና ግንቦችን ሠራ፥


ኢዮአታምም በአምላኩ በጌታ ፊት መንገዱን አቅንቶአልና በረታ።


አሞናውያንም ለዖዝያን ገበሩ፤ እጅግም በርትቶ ነበርና ዝናው እስከ ግብጽ መግቢያ ድረስ ተሰማ።


Follow us:

Advertisements


Advertisements