Biblia Todo Logo
Online Bible

- Advertisements -




1 ነገሥት 20:9 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

9 ስለዚህም አክዓብ ለቤንሀዳድ መልእክተኞች “ለጌታዬ ለንጉሡ፥ ከዚህ በፊት ባቀረብክልኝ ጥያቄ ተስማምቼ ነበር፤ አሁን ባቀረብክልኝ በሁለተኛው ጥያቄ ግን ልስማማበት አልችልም ብሏል ብላችሁ ንገሩት” አላቸው። መልእክተኞቹም ተመልሰው በመሄድ መልሱን ነገሩት፤

See the chapter Copy

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

9 ስለዚህ ለቤን ሃዳድ መልእክተኞች፣ “ለጌታዬ ለንጉሡ፣ ‘እኔ ባሪያህ በመጀመሪያ ያልኸኝን ሁሉ አደርጋለሁ፤ ያሁኑን ጥያቄህን ግን ልፈጽመው አልችልም’ ብላችሁ ንገሩት” አላቸው። መልእክተኞቹም ይህንኑ ይዘው ተመለሱ።

See the chapter Copy

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

9 ስለዚህም አክዓብ ለቤንሀዳድ መልእክተኞች “ለጌታዬ ለንጉሡ፥ ‘ከዚህ በፊት ባቀረብክልኝ ጥያቄ ተስማምቼ ነበር፤ አሁን ባቀረብክልኝ በሁለተኛው ጥያቄ ግን ልስማማበት አልችልም ብሎአል’ ብላችሁ ንገሩት” አላቸው። መልእክተኞቹም ተመልሰው በመሄድ መልሱን ነገሩት፤

See the chapter Copy

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

9 የዚ​ያች ደብ​ዳ​ቤም ቃል እን​ዲህ ይላል፥ “ጾምን ጹሙ፤ ናቡ​ቴ​ንም በሕ​ዝቡ መካ​ከል በከ​ፍ​ተኛ ቦታ አስ​ቀ​ም​ጡት፤

See the chapter Copy

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

9 በደብዳቤውም “ስለ ጾም አዋጅ ንገሩ፤ ናቡቴንም በሕዝቡ ፊት አስቀምጡት፤

See the chapter Copy




1 ነገሥት 20:9
3 Cross References  

በዚህም ምክንያት ንጉሥ አሳ በቤተ መቅደስና በቤተ መንግሥቱ የተረፈውን ወርቅና ብር ሁሉ በማውጣት በባለሟሎቹ እጅ፥ በደማስቆ ከተማ ለነበረው የጣብሪሞን ልጅ፥ የሔዝዮን የልጅ ልጅ ለሆነው ለሶርያ ንጉሥ ቤንሀዳድ ስጦታ አድርጎ ላከለት፤ ከስጦታውም ጋር እንዲህ የሚል መልእክት ነበረ፤


ሽማግሌዎቹና ሕዝቡም “እርሱ ለሚልህ ነገር ሁሉ ግምት አትስጠው፤ እሺም አትበለው” አሉት።


ቤንሀዳድም “በሰማርያ ለያንዳንዱ ወታደር አንዳንድ ጭብጥ ዐፈር ሊዳረስ እስከማይችል ድረስ ብዙ ወታደሮችን ባላሰልፍ አማልክት ይቅሠፉኝ!” ብሎ የዛቻ መልእክቱን መልሶ ላከበት።


Follow us:

Advertisements


Advertisements