Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዘኍል 21:20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

20 ከባ​ሞ​ትም ምድረ በዳ​ውን ከላይ ወደ​ሚ​መ​ለ​ከ​ተው ወደ ፈስጋ ተራራ ራስ በሞ​ዓብ በረሃ ወዳ​ለው ወደ ያኒን ሸለቆ ተጓዙ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

20 ከባሞትም ፈስጋ ላይ ሆኖ ምድረ በዳው ቍልቍል ወደሚታይበት በሞዓብ ወደሚገኘው ሸለቆ ተጓዙ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

20 ከባሞትም ምድረ በዳውን ከላይ ወደሚመለከተው ወደ ፈስጋ ተራራ ራስ በሞዓብ በረሀ ወዳለው ሸለቆ ተጓዙ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

20 ከባሞትም ተነሥተው በሞአባውያን ግዛት ውስጥ ወዳለው ሸለቆ ተጓዙ፤ ይህም ሸለቆ የሚገኘው ከፒስጋ ተራራ ግርጌ በበረሓው ትይዩ ነው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

20 ከባሞትም ምድረ በዳውን ከላይ ወደሚመለከተው ወደ ፈስጋ ተራራ ራስ በሞዓብ በረሀ ወዳለው ሸለቆ ተጓዙ።

Ver Capítulo Copiar




ዘኍል 21:20
11 Referencias Cruzadas  

ከዚ​ያ​ችም ምንጭ ወደ መን​ተ​ና​ይን ተጓዙ፤ ከመ​ን​ተ​ና​ይ​ንም ወደ ነሃ​ል​ያል፥ ከነ​ሃ​ል​ያ​ልም ወደ ባሞት፥


እስ​ራ​ኤ​ልም ወደ አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያን ንጉሥ ወደ ሴዎን በሰ​ላም ቃል እን​ዲህ ብሎ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ላከ፤


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ተጓዙ፤ በኢ​ያ​ሪኮ በኩል በዮ​ር​ዳ​ኖስ አጠ​ገብ በሞ​ዓብ ምዕ​ራ​ብም ሰፈሩ።


በሜዳ ወደ ተገ​ነባ ግንብ ራስ ላይም ወሰ​ደው፤ አዞ​ረ​ውም፤ ሰባ​ትም መሠ​ዊ​ያ​ዎች ሠራ፤ በየ​መ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ላይ አንድ ወይ​ፈን፥ አን​ድም አውራ በግ አሳ​ረገ።


ባላ​ቅም በለ​ዓ​ምን በም​ድረ በዳ ወደ ተከ​በ​በው ወደ ፌጎር ተራራ ወሰ​ደው።


በሞ​ዓብ ሜዳ ላይ በዮ​ር​ዳ​ኖስ አጠ​ገብ በኢ​ያ​ሪኮ ፊት ለፊት ሲቈ​ጥሩ፥ ሙሴና ካህኑ አል​ዓ​ዛር የቈ​ጠ​ሩ​አ​ቸው የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እነ​ዚህ ናቸው።


በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ በሞ​ዓብ ምድር ሙሴ እን​ዲህ ብሎ ይህን ሕግ ይገ​ልጥ ጀመር፦


ይህን ዮር​ዳ​ኖ​ስን አት​ሻ​ገ​ር​ምና ወደ ተራ​ራው ራስ ውጣ፤ ዐይ​ን​ህ​ንም ወደ ባሕር ወደ መስ​ዕም፥ ወደ አዜ​ብም ወደ ምሥ​ራ​ቅም አን​ሥ​ተህ በዐ​ይ​ንህ ተመ​ል​ከት።


ሙሴም ከሞ​ዓብ ሜዳ በኢ​ያ​ሪኮ ፊት ለፊት ወዳ​ለው ወደ ናባው ተራራ ወደ ፈስጋ ራስ ወጣ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እስከ ዳን ድረስ ያለ​ውን የገ​ለ​ዓ​ድን ምድር አሳ​የው፤


በም​ሥ​ራ​ቅም በኩል በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ መሿ​ለ​ኪያ ካለው ከአ​ሴ​ዶን ተራራ በታች ያለ​ውን ዓረባ ሁሉ ወሰዱ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos