Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ነህምያ 6:10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

10 እኔም ወደ መሔ​ጣ​ብ​ኤል ልጅ ወደ ዶልያ ልጅ ወደ ሴሜይ ቤት ገባሁ፤ እር​ሱም ተዘ​ግቶ ነበ​ርና፥ “በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በመ​ቅ​ደሱ ውስጥ እን​ግባ፤ የመ​ቅ​ደ​ሱ​ንም ደጆች እን​ዝጋ፤ እነ​ርሱ በሌ​ሊት ይገ​ድ​ሉህ ዘንድ ይመ​ጣ​ሉና” አለኝ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

10 አንድ ቀን ቤቱ በላዩ ላይ ተዘግቶበት ወደ ነበረው ወደ መሄጣብኤል ልጅ ወደ ድላያ ልጅ ወደ ሸማያ ሄድሁ፤ እርሱም፣ “ሰዎች ሊገድሉህ ይመጣሉ፤ በርግጥም በሌሊት ሊገድሉህ ይመጣሉ፤ በእግዚአብሔር ቤት ባለው በቤተ መቅደሱ ውስጥ እንገናኝ፤ የቤተ መቅደሱንም በሮች እንዝጋቸው” አለኝ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

10 እኔም ወደ ሜሔጣብኤል ልጅ፥ ወደ ዴላያ ልጅ፥ ወደ ሼማዕያ ቤት ሄድሁ፤ እርሱም ተዘግቶ ነበርና፦ “በእግዚአብሔር ቤት፥ በመቅደሱ ውስጥ እንገናኝ፥ የመቅደሱንም በሮች እንዝጋ፤ ሊገድሉህ ይመጣሉና፥ በሌሊት ሊገድሉህ ይመጣሉና” አለ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

10 በዚህም ጊዜ ከቤቱ እንዳይወጣ ተዘግቶበት ወደነበረው የመሄጣብኤል የልጅ ልጅ ወደ ሆነው ወደ ደላያ ልጅ ሸማዕያ ዘንድ ሄድኩ፤ እርሱም “በሌሊት ሊገድሉህ ስለሚመጡ አንተና እኔ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ገብተን በሮቹን በመዝጋት እንደበቅ” አለኝ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

10 እኔም ወደ መሔጣብኤል ልጅ ወደ ድላያ ልጅ ወደ ሸማያ ቤት ገባሁ፥ እርሱም ተዘግቶ ነበርና፦ በእግዚአብሔር ቤት በመቅደሱ ውስጥ እንገናኝ የመቅደሱንም ደጆች እንዝጋ፥ እነርሱ መጥተው ይገድሉሃልና፥ በሌሊትም ይገድሉህ ዘንድ ይመጣሉና አለ።

Ver Capítulo Copiar




ነህምያ 6:10
21 Referencias Cruzadas  

ኤር​ም​ያ​ስም ባሮ​ክን እን​ዲህ ሲል አዘ​ዘው፥ “እኔ እስ​ረኛ ነኝ፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤትም እገባ ዘንድ አል​ች​ልም።


ከተ​ማ​ውም ሁሉ ታወከ፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ እየ​ሮጡ ሄደው ጳው​ሎ​ስን ጐት​ተው ከቤተ መቅ​ደስ አወ​ጡት፤ በሩ​ንም ሁሉ ዘጉ።


ሥራው ክፉ የሆነ ሁሉ ብር​ሃ​ንን ይጠ​ላ​ልና፤ ክፉም ስለ​ሆነ ሥራው እን​ዳ​ይ​ገ​ለ​ጥ​በት ወደ ብር​ሃን አይ​መ​ጣም።


“የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።


በመሠዊያዬ ላይ እሳትን በከንቱ እንዳታቃጥሉ ከእናንተ ዘንድ ደጅ የሚዘጋ ሰው ምነው በተገኘ! በእናንተ ደስ አይለኝም፥ ቍርባንንም ከእጃችሁ አልቀበልም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።


መን​ፈ​ስም ወደ እኔ መጣ፤ በእ​ግ​ሬም አቆ​መኝ፤ ተና​ገ​ረ​ኝም እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “ሂድ ገብ​ተህ ቤት​ህን ዝጋ።


በክፉዎች አፍ የሀገር ወጥመድ አለ፥ የጻድቃን ዕውቀት ግን መልካም ጎዳና ናት።


ነፍ​ሴ​ንም የሚ​ሹ​አት በረ​ቱ​ብኝ፥ መከ​ራ​ዬ​ንም የሚ​ፈ​ልጉ ከን​ቱን ተና​ገሩ፥ ሁል​ጊ​ዜም ያጠ​ፉኝ ዘንድ በሽ​ን​ገላ ይመ​ክ​ራሉ።


እስከ መቼ በነ​ፍሴ ኀዘ​ንን አኖ​ራ​ለሁ? እስከ መቼ ልቤ ሁል​ጊዜ ትጨ​ነ​ቅ​ብ​ኛ​ለች? እስከ መቼ ጠላ​ቶች በላዬ ይታ​በ​ያሉ?


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ልኮት እን​ዳ​ል​ነ​በረ፥ በእኔ ላይ ግን ትን​ቢት እንደ ተና​ገረ፥ እነሆ፥ ዐወ​ቅሁ፤ ጦብ​ያና ሰን​ባ​ላ​ጥም ገዝ​ተ​ውት ነበር።


ከኤ​ራም ልጆ​ችም አል​ዓ​ዛር፥ ይሲያ፥ ሚል​ክያ፥ ሰማያ፥ ስም​ዖን፥


ወደ አለ​ቆ​ቹም ወደ አል​ዓ​ዛር፥ ወደ አር​ኤል፥ ወደ ሰማ​አያ፥ ወደ ሀሎ​ናም፥ ወደ ያሪብ፥ ወደ ሄል​ና​ታን፥ ወደ ናታን፥ ወደ ዘካ​ር​ያስ፥ ወደ ሜሱ​ላም፥ ደግ​ሞም ወደ ዐዋ​ቂ​ዎቹ ወደ ዮያ​ሪ​ብና ወደ ሄል​ና​ታን ላክሁ።


ደግ​ሞም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ደጆች ዘግ​ተ​ዋል፤ መብ​ራ​ቶ​ቹ​ንም አጥ​ፍ​ተ​ዋል፤ በመ​ቅ​ደ​ሱም ውስጥ ለእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ አላ​ጠ​ኑም፤ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ው​ንም መሥ​ዋ​ዕት አላ​ቀ​ረ​ቡም።


በመ​ን​ግ​ሥ​ቱም በጸና ጊዜ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ደጆች ከፈተ፤ አደ​ሳ​ቸ​ውም።


አካ​ዝም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ዕቃ​ዎች ሁሉ ወስዶ ሰባ​በ​ራ​ቸው፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቤት ደጆች ዘጋ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ማዕ​ዘን ሁሉ ለራሱ መሠ​ዊያ ሠራ።


በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ስድ​ስት ዓመት ሸሸ​ገ​ችው። ጎቶ​ል​ያም በሀ​ገሩ ላይ ነገ​ሠች።


የአ​ክ​ዓ​ብን ቤት ሁሉ ታጠ​ፋ​ለህ፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ዘንድ አጥር ተጠ​ግቶ እስ​ከ​ሚ​ሸን የቀ​ረ​በ​ውን ሁሉና ከእ​ነ​ርሱ የቀ​ረ​ውን ሁሉ ታጠ​ፋ​ለህ።


በቤ​ቱም ግንብ ዙሪያ፥ በመ​ቅ​ደ​ሱና በቅ​ድ​ስተ ቅዱ​ሳኑ ግንብ ዙሪያ ደርብ ሠራ፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ጓዳ​ዎች አደ​ረገ።


የአ​ክ​ቦር ልጅ በአ​ል​ሐ​ና​ንም ሞተ፤ በእ​ር​ሱም ፈንታ አዳር ነገሠ፤ የከ​ተ​ማ​ውም ስም ፎጎር ነው፤ ሚስ​ቱም የሜ​ዛ​አብ ልጅ መጥ​ሬድ የወ​ለ​ደ​ቻት ምኤ​ጠ​ብ​ኤል ትባ​ላ​ለች።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios