Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዘሌዋውያን 27:18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

18 እር​ሻ​ው​ንም ከኢ​ዮ​ቤ​ልዩ ዓመት በኋላ ቢሳል፥ ካህኑ እስከ ኢዮ​ቤ​ልዩ ዓመት ድረስ እንደ ቀሩት ዓመ​ታት ገን​ዘ​ቡን ይቈ​ጥ​ር​ለ​ታል፤ ከግ​ም​ቱም ይጐ​ድ​ላል።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

18 ዕርሻውን የሚቀድሰው ከኢዮቤልዩ በኋላ ከሆነ ግን፣ ካህኑ ዋጋውን የሚተምነው እስከሚመጣው የኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ ባሉት ዓመታት ቍጥር ልክ ነው፤ የተተመነውም ዋጋ ይቀነሳል።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

18 ነገር ግን እርሻውን ከኢዮቤልዩ ዓመት በኋላ ቢቀድስ፥ ካህኑ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ እንደ ቀሩት ዓመታት ቊጥር ገንዘቡን ያስላልህስ፤ ከዚያም ከግምትህ ላይ ይቀነሳል።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

18 መሬቱን የሰጠው የኢዮቤልዩ ዓመት ካለፈ ዘግይቶ ከሆነ ግን ካህኑ እስከ ተከታዩ የኢዮቤልዩ ዓመት ያለውን ቀሪ ጊዜ በመገመት ዋጋው እንዲቀነስ ያድርግ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

18 እርሻውንም ከኢዮቤልዩ ዓመት በኋላ ቢቀድስ፥ ካህኑ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ እንደ ቀሩት ዓመታት ገንዘቡን ይቈጥርለታል፤ ከግምቱም ይጐድላል።

Ver Capítulo Copiar




ዘሌዋውያን 27:18
7 Referencias Cruzadas  

የሽ​ያ​ጩን ዘመን ቈጥሮ የቀ​ረ​ውን ወደ ገዛው ሰው ይመ​ልስ፤ እር​ሱም ወደ ርስቱ ይመ​ለስ።


“ሰውም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቅዱስ ይሆን ዘንድ ቤቱን ቢቀ​ድስ፥ ካህኑ መል​ካም ወይም ክፉ እንደ ሆነ ይገ​ም​ተ​ዋል፤ ካህ​ኑም እን​ደ​ሚ​ገ​ም​ተው መጠን እን​ዲሁ ይቆ​ማል።


እር​ሻ​ው​ንም ከኢ​ዮ​ቤ​ልዩ ዓመት ጀምሮ ቢሳል፥ እንደ ግምቱ መጠን ይቆ​ማል።


እር​ሻ​ው​ንም የተ​ሳለ ሰው ይቤ​ዠው ዘንድ ቢወ​ድድ፥ ከግ​ምቱ ገን​ዘብ በላይ አም​ስ​ተኛ እጅ ይጨ​ምር፤ ለእ​ር​ሱም ይሆ​ናል።


ካህኑ እስከ ኢዮ​ቤ​ልዩ ዓመት ድረስ የግ​ም​ቱን ዋጋ ይቈ​ጥ​ር​ለ​ታል፤ በዚ​ያም ቀን ግም​ቱን እንደ ተቀ​ደሰ ነገር ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይሰ​ጣል።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos