Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ዘሌዋውያን 22:23 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

23 በሬው፥ ወይም በጉ ጆሮው፥ ወይም ጅራቱ የተ​ቈ​ረጠ ቢሆን፥ ቈጥ​ረህ የራ​ስህ ገን​ዘብ አድ​ር​ገው እንጂ ለስ​እ​ለት አይ​ቀ​በ​ል​ህም።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

23 አካሉ ከመጠን በላይ የረዘመን ወይም ያጠረን በሬ ወይም በግ የበጎ ፈቃድ ስጦታ አድርጋችሁ ማቅረብ ትችላላችሁ፤ ይሁን እንጂ ስእለት ለመፈጸም ተቀባይነት አይኖረውም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

23 የበሬው ወይም የበጉ የአካሉ ክፍል ረጅም ወይም አጭር ቢሆን፥ ለፈቃድ መሥዋዕት ማቅረብ ትችላለህ፤ ለስእለት ግን አይሠምርም።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

23 አካሉ የጐደለ ወይም ቅርጹ የተበላሸ እንስሳ የበጎ ፈቃድ መሥዋዕት ሆኖ ሊቀርብ ይችላል፤ ነገር ግን ስእለት የተፈጸመለት ሰው መሥዋዕት አድርጎ ሊያቀርበው አይችልም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

23 በሬው ወይም በጉ የተጨመረበት ወይም የጐደለበት ነገር ቢሆን፥ ለፈቃድ መሥዋዕት ማቅረብ ትችላለህ፤ ለስእለት ግን አይሠምርም።

Ver Capítulo Copiar




ዘሌዋውያን 22:23
7 Referencias Cruzadas  

ንጹሕ ያል​ሆነ ሰው ሁሉ አይ​ቅ​ረብ፤ ዕውር፥ ወይም አን​ካሳ፥ ወይም አፍ​ንጫ ደፍ​ጣጣ፥ ወይም ጆሮ ቈራጣ፥


ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆ​ችም ያመጡ ዘንድ ልባ​ቸው ያስ​ነ​ሣ​ቸው ወን​ዶ​ችና ሴቶች ሁሉ ሙሴ ይሠራ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ላዘ​ዘው ሥራ ሁሉ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስጦታ በፈ​ቃ​ዳ​ቸው አመጡ።


ዕውር፥ ወይም ሰባራ፥ ወይም ምላሱ የተ​ቈ​ረጠ፥ ወይም የሚ​መ​ግል ቍስል ያለ​በት፥ ወይም እከ​ካም፥ ወይም ቋቍ​ቻም ቢሆን፥ እነ​ዚ​ህን ሁሉ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አታ​ቅ​ርቡ፤ እነ​ዚ​ህ​ንም ለእ​ሳት ቍር​ባን በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ለእ​ግ​ዚ​አ​ሔር አታ​ሳ​ርጉ።


የተ​ቀ​ጠ​ቀ​ጠ​ውን፥ ወይም የተ​ሰ​በ​ረ​ውን፥ ወይም የተ​ቈ​ረ​ጠ​ውን ወይም የተ​ሰ​ነ​ጋ​ውን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አታ​ቅ​ርቡ፤ በም​ድ​ራ​ች​ሁም እነ​ዚ​ህን አት​ሠዉ።


ነው​ረኛ ወይም አን​ካሳ ወይም ዕውር ቢሆን፥ ወይም አን​ዳች ክፉ ነውር ቢኖ​ረው፥ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አት​ሠ​ዋው።


“በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የተ​ጠላ ነውና ነውር ወይም ክፉ ነገር ያለ​በ​ትን በሬ ወይም በግ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አት​ሠዋ።


ዕውር መሥዋዕትንም ስታቀርቡ ይህ ክፉ አይደለምን? አንካሳውንና የታመመውን ስታቀርቡ ይህ ክፉ አይደለምን? ያንን ለአለቃህ አቅርብ፣ በውኑ በአንተ ደስ ይለዋልን? ወይስ ፊትህን ይቀበላልን? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios