Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ሰቈቃወ 2:9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

9 ጤት። በሮ​ችዋ በመ​ሬት ውስጥ ሰጠሙ፤ መወ​ር​ወ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ዋም ተሰ​በሩ፤ ንጉ​ሥ​ዋና አለ​ቃዋ በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል አሉ፤ ሕግም የለም። ነቢ​ያ​ቷም ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ራእይ አላ​ዩም።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

9 በሮቿ ወደ ምድር ሰመጡ፤ የብረት መወርወሪያዎቻቸውን ሰባበረ፤ አጠፋቸውም፤ ንጉሧና መሳፍንቷ በአሕዛብ መካከል ተማርከው ተሰድደዋል፤ ሕጉ ከእንግዲህ አይኖርም፤ ነቢያቷም ከእንግዲህ፣ ከእግዚአብሔር ራእይ አያገኙም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

9 ጤት። በሮችዋ በመሬት ውስጥ ሰጠሙ፥ መወርወሪያዎችዋን አጠፋ፤ ሰበረም፤ ንጉሥዋና አለቆችዋ ሕግ በሌለባቸው በአሕዛብ መካከል አሉ፥ ነቢዮችዋም ከእግዚአብሔር ዘንድ ራእይ አላገኙም።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

9 የቅጽር በሮች ከመሬት በታች ተቀበሩ፤ መወርወሪያዎቻቸውም ተሰባብረው ወደቁ፤ ንጉሡና መሳፍንቱ አሁን በአሕዛብ መካከል በስደት ላይ ናቸው፤ የኦሪት ሕግ ትምህርት ከእንግዲህ ወዲህ አይሰጥም፤ ነቢያትም ከእግዚአብሔር ዘንድ ራእይ አይገለጥላቸውም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

9 ጤት። በሮችዋ በመሬት ውስጥ ሰጠሙ፥ መወርወሪያዎችዋን አጠፋ ሰበረም፥ ንጉሥዋና አለቆችዋ ሕግ በሌለባቸው በአሕዛብ መካከል አሉ፥ ነቢያቶችዋም ከእግዚአብሔር ዘንድ ራእይ አላገኙም።

Ver Capítulo Copiar




ሰቈቃወ 2:9
27 Referencias Cruzadas  

ድን​ጋጤ በድ​ን​ጋጤ ላይ ይመ​ጣል፤ ወዮታ በወ​ዮታ ላይ ይከ​ተ​ላል፤ ከነ​ቢ​ዩም ዘንድ ራእ​ይን ይሻሉ፤ ከካ​ህ​ኑም ዘንድ ሕግ፥ ከሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎ​ችም ዘንድ ምክር ይጠ​ፋል።


የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ያለ ንጉ​ሥና ያለ አለቃ፥ ያለ መሥ​ዋ​ዕ​ትና ያለ ምሥ​ዋዕ፤ ያለ ካህ​ንና ያለ ራእይ፤ ያለ ኤፉ​ድና ያለ ተራ​ፊም ብዙ ወራት ይቀ​መ​ጣ​ሉና፤


እነ​ር​ሱም፥ “በዚያ ስፍራ ያሉት ከም​ርኮ የተ​ረ​ፉት ቅሬ​ታ​ዎች በታ​ላቅ መከ​ራና ስድብ አሉ፤ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ቅጥር ፈር​ሶ​አል፥ በሮ​ች​ዋም በእ​ሳት ተቃ​ጥ​ለ​ዋል” አሉኝ።


እስ​ራ​ኤ​ልም ብዙ ዘመን እው​ነ​ተ​ኛ​ውን አም​ላክ ሳያ​መ​ልኩ፥ ያለ አስ​ተ​ማ​ሪም ካህን፥ ያለ ሕግም ይኖ​ራሉ።


የባ​ቢ​ሎን ተዋ​ጊ​ዎች መዋ​ጋ​ትን ትተ​ዋል፤ በአ​ም​ባ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም ውስጥ ተቀ​ም​ጠ​ዋል፤ ኀይ​ላ​ቸ​ውም ጠፍ​ቶ​አል፤ እንደ ሴቶ​ችም ሆነ​ዋል፤ ማደ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ዋም ነድ​ደ​ዋል፤ መወ​ር​ወ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ዋም ተሰ​ብ​ረ​ዋል።


እኔ ግን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ደስ ይለ​ኛል፥ ለያ​ዕ​ቆ​ብም አም​ላክ እዘ​ም​ራ​ለሁ፥


“እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አን​ተን፥ በአ​ን​ተም ላይ የም​ት​ሾ​ማ​ቸ​ውን አለ​ቆ​ች​ህን አን​ተና አባ​ቶ​ችህ ወዳ​ላ​ወ​ቃ​ች​ኋ​ቸው ሕዝብ ይወ​ስ​ድ​ሃል፤ በዚ​ያም ሌሎ​ችን የእ​ን​ጨ​ትና የድ​ን​ጋይ አማ​ል​ክ​ትን ታመ​ል​ካ​ለህ።


መረ​ቤ​ንም በእ​ርሱ ላይ እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ በወ​ጥ​መ​ድም ይያ​ዛል፤ ወደ ባቢ​ሎ​ንም አመ​ጣ​ዋ​ለሁ፤ በእ​ኔም ላይ ስላ​ደ​ረ​ገው ዐመፅ በዚያ ከእ​ርሱ ጋር እፋ​ረ​ዳ​ለሁ።


መረ​ቤ​ንም በእ​ርሱ ላይ እዘ​ረ​ጋ​ለሁ፤ በወ​ጥ​መ​ዴም ይያ​ዛል፤ ወደ ከለ​ዳ​ው​ያ​ንም ምድር ወደ ባቢ​ሎን አመ​ጣ​ዋ​ለሁ፤ ሆኖም አያ​ያ​ትም፤ በዚ​ያም ይሞ​ታል።


ሬስ። ስለ እርሱ፥ “በአ​ሕ​ዛብ ውስጥ በጥ​ላው በሕ​ይ​ወት እን​ኖ​ራ​ለን” ያል​ነው፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ቀባ፥ የሕ​ይ​ወ​ታ​ችን እስ​ት​ን​ፋስ፥ በወ​ጥ​መ​ዳ​ቸው ተያዘ።


ሳም​ኬት። እና​ንተ ከር​ኩ​ሳን ራቁ፥ አስ​ተ​ም​ሩ​አ​ቸው፤ ራቁ፥ ራቁ በሉ​አ​ቸው፤ አት​ን​ኩ​አ​ቸ​ውም። ታው​ከ​ዋ​ልና ዳግ​መኛ እን​ዳ​ይ​ኖ​ሩ​ባት ለአ​ሕ​ዛብ ንገ​ሩ​አ​ቸው።


ጋሜል። ይሁዳ ስለ ውር​ደ​ቷና ስለ ባር​ነቷ ብዛት ተሰ​ደ​ደች፤ በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ተቀ​መ​ጠች፤ ዕረ​ፍ​ትም አላ​ገ​ኘ​ችም፤ የሚ​ያ​ሳ​ድ​ዱ​አት ሁሉ በሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቁ​አት መካ​ከል ያዙ​ዋት።


ከአ​ዛ​ዦ​ችም አለቃ ጋር የነ​በ​ረው የከ​ለ​ዳ​ው​ያን ሠራ​ዊት ሁሉ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን ቅጥር ሁሉ ዙሪ​ያ​ዋን አፈ​ረሱ።


ከለ​ዳ​ው​ያ​ንም የን​ጉ​ሡ​ንና የሕ​ዝ​ቡን ቤቶች በእ​ሳት አቃ​ጠሉ፤ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም ቅጥር አፈ​ረሱ።


በሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስም በዐ​ሥራ አን​ደ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥት በአ​ራ​ተ​ኛው ወር፥ ከወ​ሩም በዘ​ጠ​ነ​ኛው ቀን ከተ​ማ​ዪቱ ተለ​ያ​የች።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ አለኝ፥ “ነቢ​ያቱ በስሜ የሐ​ሰት ትን​ቢት ይና​ገ​ራሉ፤ አላ​ክ​ኋ​ቸ​ውም፤ አላ​ዘ​ዝ​ኋ​ቸ​ውም፤ አል​ተ​ና​ገ​ር​ኋ​ቸ​ውም፤ የሐ​ሰ​ቱን ራእይ፥ ምዋ​ር​ት​ንም፥ ከን​ቱ​ንም ነገር፥ በል​ባ​ቸ​ውም የፈ​ጠ​ሩ​ትን ይተ​ነ​ብ​ዩ​ላ​ች​ኋል።”


የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስ​ንም ልጆች በፊቱ ገደ​ሉ​አ​ቸው፤ የሴ​ዴ​ቅ​ያ​ስ​ንም ዐይ​ኖች አወጡ፤ በሰ​ን​ሰ​ለ​ትም አሰ​ሩት፤ ወደ ባቢ​ሎ​ንም ወሰ​ዱት።


ኀያል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ትን​ቢት የሚ​ና​ገ​ሩ​ላ​ች​ሁን የነ​ቢ​ያ​ትን ቃል አት​ስሙ፤ ከን​ቱ​ነ​ትን ያስ​ተ​ም​ሩ​አ​ች​ኋል፤ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አፍ ሳይ​ሆን ከገዛ ልባ​ቸው የወ​ጣ​ውን ራእይ ይና​ገ​ራሉ።


ጦር በከ​ተ​ማው ደከ​መች፤ ከእ​ጁም ይለ​ያ​ታል፤ ከሥ​ራ​ቸ​ውም ፍሬ ይበ​ላሉ።


የደ​ማ​ስ​ቆ​ንም ቍል​ፎች እሰ​ብ​ራ​ለሁ፤ በአ​ዎን ሸለቆ የሚ​ኖ​ሩ​ት​ንም ሰዎች አጠ​ፋ​ለሁ፤ የካ​ራን ሰዎች ወገ​ኖ​ች​ንም እቈ​ራ​ር​ጣ​ለሁ፤ የሶ​ርያ ሕዝ​ብም ወደ ቂር ይማ​ረ​ካሉ፤” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በጎ ያደ​ር​ግ​ልህ ዘንድ፥ ያበ​ዛ​ህም ዘንድ ደስ ይለው እንደ ነበረ፥ እን​ዲሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሲያ​ጠ​ፋህ፥ ሲያ​ፈ​ር​ስ​ህም ደስ ይለ​ዋል፤ ትወ​ር​ሳ​ትም ዘንድ ከም​ት​ገ​ባ​ባት ምድር ትነ​ቀ​ላ​ለህ ።


ሳኦ​ልም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ጠየቀ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሕ​ልም አላ​ሚ​ዎች፥ ወይም በነ​ጋ​ሪ​ዎች፥ ወይም በነ​ቢ​ያት አል​መ​ለ​ሰ​ለ​ትም።


ከተ​ሞ​ችም ባድማ ይሆ​ናሉ፤ ቤቶ​ችም ባዶ ሆነው ይቀ​ራሉ፤ ይጠ​ፋ​ሉም።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios