Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ኢያሱ 6:19 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

19 ነገር ግን ብርና ወርቅ ሁሉ፥ የና​ስና የብ​ረ​ትም ዕቃ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ቀ​ደሰ ይሁን፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ግምጃ ቤት ይግባ።”

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

19 ብሩና ወርቁ እንዲሁም የናሱና የብረቱ ዕቃ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ስለ ሆነ፣ ወደ እግዚአብሔር ግምጃ ቤት ይግባ።”

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

19 ነገር ግን ብርና ወርቅ ሁሉ የናስና የብረትም ዕቃ ለጌታ የተቀደሰ ይሁን፤ ወደ ጌታም ግምጃ ቤት ይግባ።”

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

19 ብርና ወርቅ፥ ከነሐስ ወይም ከብረት የተሠራ ማናቸውም ነገር ለእግዚአብሔር የተለየ ይሁን፤ እርሱም በእግዚአብሔር የዕቃ ግምጃ ቤት መቀመጥ አለበት።”

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

19 ነገር ግን ብርና ወርቅ ሁሉ የናስና የብረትም ዕቃ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ይሁን፥ ወደ እግዚአብሔርም ግምጃ ቤት ይግባ።

Ver Capítulo Copiar




ኢያሱ 6:19
25 Referencias Cruzadas  

የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው “የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም፤” አሉ።


ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ሌዋ​ው​ያ​ንም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በሚ​ሆኑ ቤተ መዛ​ግ​ብ​ትና በን​ዋየ ቅድ​ሳቱ ቤተ መዛ​ግ​ብት ላይ ተሹ​መው ነበር።


ኢየሱስም በመዝገብ አንጻር ተቀምጦ ሕዝቡ በመዝገብ ውስጥ ገንዘብ እንዴት እንዲጥሉ ያይ ነበር፤ ብዙ ባለ ጠጎችም ብዙ ይጥሉ ነበር፤


ሌዋ​ው​ያ​ኑም ዐሥ​ራ​ቱን በተ​ቀ​በሉ ጊዜ የአ​ሮን ልጅ ካህኑ ከሌ​ዋ​ው​ያን ጋር ይሁን፤ ሌዋ​ው​ያ​ኑም የዐ​ሥ​ራ​ቱን ዐሥ​ራት ወደ አም​ላ​ካ​ችን ቤት ወደ ጓዳ​ዎች ወደ ዕቃ ቤት ያም​ጡት።


ንጉ​ሡም ዳዊት ከአ​ሕ​ዛብ ሁሉ ከኤ​ዶ​ምና ከሞ​ዓብ፥ ከአ​ሞ​ንም ልጆች፥ ከፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም፥ ከአ​ማ​ሌ​ቅም ከማ​ረ​ከው ብርና ወርቅ ጋር እነ​ዚ​ህን ደግሞ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀደሰ።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤተ መዛ​ግ​ብት ሁሉ የን​ጉ​ሡ​ንም ቤተ መዛ​ግ​ብት ከዚያ አወጣ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እንደ ተና​ገ​ረው የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ሰሎ​ሞን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መቅ​ደስ የሠ​ራ​ውን የወ​ር​ቁን ዕቃ ሁሉ ሰባ​በረ።


እን​ዲ​ሁም ንጉሡ ሰሎ​ሞን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት የአ​ሠ​ራው ሥራ ሁሉ ተፈ​ጸመ። አባ​ቱም ዳዊት የቀ​ደ​ሰ​ውን፥ ራሱም የቀ​ደ​ሰ​ውን፥ የብ​ርና የወ​ርቅ ዕቃ ሰሎ​ሞን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ውስጥ በነ​በሩ ግምጃ ቤቶች አገባ።


እር​ሱ​ንም ንጉሥ ዳዊት ከሀ​ገ​ሮች ሁሉ አም​ጥቶ ከቀ​ደ​ሰው ከወ​ር​ቁና ከብሩ ጋር ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀደሰ፤


የጽዮን ልጅ ሆይ፥ ቀንድሽን ብረት፥ ጥፍርሽንም ናስ አደርጋለሁና ተነሺ አሂጂ፥ ብዙ አሕዛብንም ታደቅቂአለሽ፥ ትርፋቸውንም ለእግዚአብሔር፥ ሀብታቸውንም ለምድር ሁሉ ጌታ ትቀድሻለሽ።


መባ​ኡ​ንና ዐሥ​ራ​ቱን፥ የተ​ቀ​ደ​ሱ​ት​ንም በእ​ም​ነት ወደ​ዚያ አገቡ። ሌዋ​ዊ​ውም ኮክ​ን​ያስ ተሾ​መ​ባ​ቸው፥ ወን​ድ​ሙም ሰሜኢ በማ​ዕ​ርግ ሁለ​ተኛ ነበረ፤


አባ​ቱም ዳዊት የቀ​ደ​ሰ​ውን፥ እር​ሱም የቀ​ደ​ሰ​ውን ወር​ቁ​ንና ብሩን፥ ልዩ ልዩ​ው​ንም ዕቃ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት​አ​ገባ።


ደግ​ሞም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አደ​ባ​ባ​ዮ​ችና በዙ​ሪ​ያው ለሚ​ሆኑ ጓዳ​ዎች፥ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ለሚ​ሆኑ ቤተ መዛ​ግ​ብት፥ ለን​ዋየ ቅድ​ሳ​ቱም ለሚ​ሆኑ ዕቃ ቤቶች፥ ለቀ​ሩ​ትም በመ​ን​ፈሱ ላሰ​በው ሁሉ ምሳ​ሌን ሰጠው።


ነቢዩ ሳሙ​ኤል፥ የቂ​ስም ልጅ ሳኦል፥ የኔ​ርም ልጅ አበ​ኔር፥ የሶ​ር​ህ​ያም ልጅ ኢዮ​አብ የቀ​ደ​ሱት የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ንዋየ ቅድ​ሳት ሁሉ ከሰ​ሎ​ሚ​ትና ከወ​ን​ድ​ሞቹ እጅ በታች ነበረ።


ይህ ሰሎ​ሚ​ትና ወን​ድ​ሞቹ፥ ንጉሡ ዳዊ​ትና የአ​ባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆች፥ ሻለ​ቆ​ችና የመቶ አለ​ቆች፥ የሠ​ራ​ዊ​ቱም አለ​ቆች፥ በቀ​ደ​ሱት በን​ዋየ ቅድ​ሳቱ ቤተ መዛ​ግ​ብት ሁሉ ላይ ተሹ​መው ነበር።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤተ መዛ​ግ​ብ​ትና የን​ጉ​ሡን ቤተ መዛ​ግ​ብት ሁሉ ወሰደ፤ ዳዊ​ትም ከሱባ ንጉሥ ከአ​ድ​ር​ዓ​ዛር ልጆች እጅ ወስዶ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ያመ​ጣ​ቸ​ውን የወ​ርቅ ጦሮ​ችና ሰሎ​ሞን የሠ​ራ​ቸ​ውን የወ​ር​ቁን ጋሻና ጦር ሁሉ ወደ ግብፅ ወሰደ።


አቤ​ሜ​ሌ​ክም ከእ​ርሱ ጋር ሰዎ​ችን ይዞ ሄደ፤ ከቤተ መዛ​ግ​ብ​ቱም በታች ወደ ነበ​ረው ወደ ንጉሥ ቤት ገባ፤ ከዚ​ያም ዕላቂ ጨር​ቅና አሮጌ ገመድ ወሰደ፥ ወደ ኤር​ም​ያ​ስም ወደ ጕድ​ጓዱ ውስጥ በገ​መድ አወ​ረ​ደው።


ወር​ቁና ብሩ፥ ናሱም፥ ብረ​ቱም፥ ቆር​ቆ​ሮ​ውም፥ እር​ሳ​ሱም፥


በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ፍሬ ሁሉ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋና ቅዱስ ይሁን።


ከሰው እስከ እን​ስሳ ምር​ኮ​አ​ቸ​ው​ንና ብዝ​በ​ዛ​ቸ​ውን ሁሉ ወሰዱ።


የማ​ረ​ኩ​ትን ምር​ኮ​ው​ንና የዘ​ረ​ፉ​ትን ወደ ሙሴና ወደ ካህኑ ወደ አል​ዓ​ዛር፥ ወደ እስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች፥ በዮ​ር​ዳ​ኖ​ስም አጠ​ገብ በኢ​ያ​ሪኮ ፊት ለፊት በሞ​ዓብ ሜዳ ወዳ​ለው ሰፈር አመጡ።


ሕዝቡ በድ​ለ​ዋል፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር የገ​ባ​ሁ​ትን ቃል ኪዳ​ኔን አፍ​ር​ሰ​ዋል፤ እርም ከሆ​ነ​ውም ነገር ሰር​ቀው ወሰዱ፤ በዕ​ቃ​ቸ​ውም ውስጥ ሸሸ​ጉት።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ ሕንጻ ወደ ኋላ እን​ዳ​ይል ዳዊት ከየ​ሀ​ገሩ በማ​ረ​ካ​ቸ​ውና በሰ​በ​ሰ​ባ​ቸው በቀ​ደ​ሳ​ቸ​ውም ላይ የተ​ሾሙ ናቸው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios