Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ኢዮብ 9:4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

4 በልቡ ጠቢብ ነው፥ ኀይ​ለ​ኛም፥ ታላ​ቅም ነው፤ ክፉስ ሆኖ በፊቱ የቆመ ማን ነው?

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

4 ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤ እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጕዳት የሄደ ማን ነው?

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

4 ልቡ ጠቢብ፥ ኃይሉም ታላቅ ነው፥ እርሱንስ ተዳፍሮ በደኅና የቆየ ማን ነው?

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

4 እግዚአብሔር ጠቢብና ኀያል ነው፤ ማነው እርሱን ተቋቊሞ ያልተሸነፈ?

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

4 ልቡ ጠቢብ፥ ኃይሉም ታላቅ ነው፥ ደፍሮትስ በደኅና የሄደ ማን ነው?

Ver Capítulo Copiar




ኢዮብ 9:4
39 Referencias Cruzadas  

እነ​ሆም፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእኛ ላይ አለቃ ነው፤ መለ​ከ​ቱ​ንም የሚ​ነፉ ካህ​ናቱ ከእኛ ጋር ናቸው፤ በእ​ና​ን​ተም ላይ ይጮ​ኻሉ። የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ሆይ፥ አይ​በ​ጃ​ች​ሁ​ምና ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ አም​ላክ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር አቷጉ።”


እን​ዲ​ህም አለ፥ “አቤቱ፥ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን አም​ላክ ሆይ፥ በሰ​ማይ ያለህ አም​ላክ አንተ አይ​ደ​ለ​ህ​ምን? የአ​ሕ​ዛ​ብ​ንስ መን​ግ​ሥ​ታት ሁሉ የም​ት​ገዛ አንተ አይ​ደ​ለ​ህ​ምን? ኀይ​ልና ችሎታ በእ​ጅህ ነው፤ ሊቋ​ቋ​ም​ህም የሚ​ችል የለም።


የጥ​በ​ቡን ኀይል ቢገ​ል​ጥ​ልህ! ባንተ ላይ ያለው እጥፍ ነውና። ያን​ጊ​ዜም ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ በበ​ደ​ልህ ያገ​ኘህ ትክ​ክል እንደ ሆነ ታው​ቃ​ለህ።


በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ጥበ​ብና ኀይል አለ፤ ለእ​ርሱ ምክ​ርና ማስ​ተ​ዋል አለው።


በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በቍጣ ትመ​ልስ ዘንድ፤ እን​ደ​ዚ​ህስ ያለ ነገር ከአ​ፍህ ታወጣ ዘንድ፤


በኀ​ይሉ ብዛት ቢመ​ጣ​ብ​ኝም እንኳ በቍ​ጣው አያ​ስ​ፈ​ራ​ራ​ኝም ነበር።


ነገር ግን ረዳት የሌ​ላ​ቸ​ውን በቍ​ጣው አጠ​ፋ​ቸው። እር​ሱም በተ​ነሣ ጊዜ ሰው በሕ​ይ​ወቱ አይ​ታ​መ​ንም።


“ጥን​ቱን መፈ​ራት በእ​ርሱ ዘንድ ያለ አይ​ደ​ለ​ምን? በከ​ፍ​ታ​ውም ሁሉን ነገር አድ​ራጊ ነው።


“እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ገ​ድ​ዋን አሳ​መረ፥ እር​ሱም ስፍ​ራ​ዋን ያው​ቃል።


“በጥ​በብ ብር​ቱና ኀያል የሆነ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፥ የዋ​ሁን ሰው እን​ደ​ማ​ይ​ጥ​ለው ዕወቅ።


በኀ​ይል ከእ​ርሱ ጋር እኩል የሚ​ሆን፥ እው​ነ​ት​ንም የሚ​ፈ​ርድ ሌላ አና​ገ​ኝም። እርሱ እን​ደ​ማ​ይ​ሰማ ታስ​ባ​ለ​ህን?


ለሴ​ቶች የፈ​ት​ልን ጥበ​ብና የተ​ለ​ያዩ የጥ​ልፍ ሥራ​ዎ​ችን ዕው​ቀት ማን ሰጠ?


የሰ​ማ​ይን ደመና በጥ​በቡ ሊቈ​ጥር የሚ​ችል ማን ነው? ሰማ​ይ​ንም ወደ ምድር ያዘ​ነ​በለ ማን ነው?


እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክንድ ያለ ክንድ አለ​ህን? ወይስ እንደ እርሱ ባለ ድምፅ ታን​ጐ​ደ​ጕ​ዳ​ለ​ህን?


የሚ​ከ​ራ​ከ​ረ​ኝና በሕ​ይ​ወት የሚ​ኖ​ርስ ማን ነው? ከሰ​ማይ በታች ያለ​ውም ሁሉ የእኔ ነው።


መቃ​ብሬ በግ​ንቡ የም​መ​ላ​ለ​ስ​በት ከተ​ማዬ ይሁን፥ ከእ​ር​ሱም ፈቀቅ አል​ልም የአ​ም​ላ​ኬን ቅዱስ ቃል አል​ካ​ድ​ሁ​ምና።


እርሱ በኀ​ይል ይይ​ዛ​ልና፤ ፍር​ዱን ማን ይቃ​ወ​ማል?


ሕዝ​ቡ​ንም እጅግ አበ​ዛ​ቸው፥ ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ይልቅ አበ​ረ​ታ​ቸው።


ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሆይ፥ ብረ​ሳሽ፥ ቀኜ ትር​ሳኝ።


በክ​ብ​ር​ህም ብዛት ጠላ​ቶ​ች​ህን አጠ​ፋህ፤ ቍጣ​ህን ሰደ​ድህ፤ እንደ ገለ​ባም በላ​ቸው።


ፈር​ዖ​ንም ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ከብት አንድ ስንኳ እን​ዳ​ል​ሞተ በአየ ጊዜ ልቡ ደነ​ደነ፤ ሕዝ​ቡ​ንም አል​ለ​ቀ​ቀም።


“እንደ ሸክላ ሠሪ ሥራ ውብ አድ​ርጌ ሠራ​ሁህ፤ ምድ​ርን የሚ​ያ​ርስ ሁል​ጊዜ ያር​ሳ​ልን? ጭቃ ሠሪ​ውን፦ ምን ትሠ​ራ​ለህ? እጅ የለ​ህ​ምና መሥ​ራት አት​ች​ልም ይለ​ዋ​ልን? ጭቃ ሠሪ​ውን ይከ​ራ​ከ​ረ​ዋ​ልን?


ባቢ​ሎን ሆይ! በመ​ከ​ራው ተይ​ዘሽ ጠፋሽ፤ አን​ቺም ይህ እን​ደ​መ​ጣ​ብሽ አላ​ወ​ቅ​ሽም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ተቃ​ው​መ​ሽ​ዋ​ልና ተገ​ኝ​ተ​ሻል፤ ተይ​ዘ​ሽ​ማል።


እግዚአብሔር ትዕግሥተኛ፥ ኃይሉም ታላቅ ነው፥ በደለኛውንም፦ ንጹሕ ነህ አይልም፣ እግዚአብሔር በወጀብና በዐውሎ ነፋስ ውስጥ መንገድ አለው፥ ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባለ​ጠ​ግ​ነት፥ ጥበ​ብና ዕው​ቀት እን​ዴት ጥልቅ ነው! ለመ​ን​ገ​ዱም ፍለጋ የለ​ውም፤ ፍር​ዱ​ንም የሚ​ያ​ው​ቀው የለም።


እን​ግ​ዲህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እና​ስ​ቀ​ና​ውን? በውኑ እኛ ከእ​ርሱ እን​በ​ረ​ታ​ለን?


በክ​ር​ስ​ቶስ እንደ አደ​ረ​ገው እንደ ከሃ​ሊ​ነቱ ታላ​ቅ​ነት በም​ና​ምን በእኛ ላይ የሚ​ያ​ደ​ር​ገው የከ​ሃ​ሊ​ነቱ ጽናት ብዛት ምን እንደ ሆነ ታውቁ ዘንድ ነው።


ይኸ​ውም በፍ​ጹም ጥበ​ብና ምክር ለእኛ አብ​ዝቶ ያደ​ረ​ገው ነው።


ብዙ ልዩ ልዩ የሆ​ነች የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክር​ስ​ቲ​ያን በኩል በሰ​ማ​ያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለ​ቆ​ችና ሥል​ጣ​ናት ትታ​ወቅ ዘንድ፤


በከ​ሃ​ሊ​ነቱ እንደ ረዳን መጠን፥ የም​ና​ስ​በ​ው​ንና የም​ን​ለ​ም​ነ​ውን ሁሉ ትሠሩ ዘንድ፥ ታበ​ዙም ዘንድ ሊያ​ጸ​ና​ችሁ ለሚ​ችል፥


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos