Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ኤርምያስ 35:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

14 የሬ​ካብ ልጅ ኢዮ​ና​ዳብ ልጆቹ የወ​ይን ጠጅ እን​ዳ​ይ​ጠጡ ያዘ​ዛ​ቸው ቃል ተፈ​ጸመ፤ ለአ​ባ​ታ​ቸ​ውም ትእ​ዛዝ ታዝ​ዘ​ዋ​ልና እስከ ዛሬ ድረስ ወይን አይ​ጠ​ጡም፤ እኔም በማ​ለዳ ስለ እና​ንተ ተና​ገ​ርሁ፤ ሆኖም አል​ሰ​ማ​ች​ሁ​ኝም።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

14 ‘የሬካብ ልጅ ኢዮናዳብ ልጆቹ የወይን ጠጅ እንዳይጠጡ አዘዛቸው፤ ይህም ትእዛዝ ተጠብቋል፤ የአባታቸውን ትእዛዝ ስለ ጠበቁ እስከ ዛሬ ድረስ የወይን ጠጅ አይጠጡም፤ እናንተ ግን እኔ ደጋግሜ ብናገራችሁም፤ አልታዘዛችሁኝም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

14 የሬካብ ልጅ ኢዮናዳብ ልጆቹን የወይን ጠጅ እንዳይጠጡ ያዘዛቸው ቃላት ተፈጸሙ፤ ለአባታቸውም ትእዛዝ ታዝዘዋልና እስከ ዛሬ ድረስ አይጠጡም፤ እኔም በማለዳ ተነሥቼ ተናገርኋቸው፤ ተናገርሁ፥ ሆኖም ግን አልሰማችሁኝም።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

14 የኢዮናዳብ ዘሮች እንኳ የወይን ጠጅ እንዳይጠጡ አባታቸው ያዘዛቸውን ቃል በመጠበቅ እነሆ እስከ አሁን ድረስ ምንም ዐይነት የወይን ጠጅ አይቀምሱም፤ እኔ ግን ሁልጊዜ በመደጋገም እነግራችኋለሁ፤ እናንተ ልትታዘዙኝ አልፈለጋችሁም፤

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

14 የሬካብ ልጅ ኢዮናዳብ ልጆቹ የወይን ጠጅ እንዳይጠጡ ያዘዛቸው ቃል ተፈጸመ፥ ለአባታቸውም ትእዛዝ ታዝዘዋልና እስከ ዛሬ ድረስ አይጠጡም፥ እኔም በማለዳ ተነሥቼ ተናግሬአችኋለሁ፥ ተናገርሁ፥ ሆኖም አልሰማችሁኝም።

Ver Capítulo Copiar




ኤርምያስ 35:14
15 Referencias Cruzadas  

አባ​ቶ​ቻ​ች​ሁን ከግ​ብፅ ምድር ከአ​ወ​ጣ​ሁ​በት ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ፥ በማ​ለዳ ተነ​ሥቼ እያ​ስ​ጠ​ነ​ቀ​ቅሁ፦ ቃሌን ስሙ በማ​ለት አስ​ጠ​ን​ቅ​ቄ​አ​ቸው ነበር።


አሁ​ንም ይህን ነገር ሁሉ ስላ​ደ​ረ​ጋ​ችሁ፥ ተና​ገ​ር​ኋ​ችሁ፤ ነገር ግን አል​ሰ​ማ​ች​ሁም፤ ጠራ​ኋ​ች​ሁም፤ ነገር ግን አል​መ​ለ​ሳ​ች​ሁም፤


እነሆ፥ መጣሁ፤ ሰውም አል​ነ​በ​ረም፤ ተጣ​ራሁ፤ የሚ​መ​ል​ስም አል​ነ​በ​ረም፤ እጄ ለማ​ዳን ጠን​ካራ አይ​ደ​ለ​ምን? ወይስ ለማ​ዳን አል​ች​ል​ምን? እነሆ፥ በገ​ሠ​ጽሁ ጊዜ ባሕ​ርን አደ​ር​ቃ​ለሁ፤ ወን​ዞ​ች​ንም ምድረ በዳ አደ​ር​ጋ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ውኃም በማ​ጣት ዐሣ​ዎ​ቻ​ቸው ይሞ​ታሉ፤ በጥ​ማ​ትም ያል​ቃሉ።


ዐመ​ፀኛ ወገን፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ ለመ​ስ​ማት እምቢ ያሉ የሐ​ሰት ልጆች ናቸ​ውና፤


ፊታ​ቸ​ው​ንም ሳይ​ሆን ጀር​ባ​ቸ​ውን ወደ እኔ መለሱ፤ እኔም በማ​ለዳ ተነ​ሥቼ ሳስ​ተ​ም​ራ​ቸው ተግ​ሣ​ጽን ይቀ​በሉ ዘንድ አል​ሰ​ሙም።


ይህም የሆ​ነው ቃሌን ስላ​ል​ሰሙ ነው፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ በማ​ለዳ ባሪ​ያ​ዎ​ችን ነቢ​ያ​ትን ወደ እነ​ርሱ ሰድ​ጃ​ለ​ሁና፤ እና​ንተ ግን አል​ሰ​ማ​ች​ሁም፤ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ነገር ግን ብዙ ዓመ​ታት ታገ​ሥ​ሃ​ቸው፤ በነ​ቢ​ያ​ት​ህም እጅ በመ​ን​ፈ​ስህ መሰ​ከ​ር​ህ​ባ​ቸው፤ አላ​ደ​መ​ጡም፤ ስለ​ዚ​ህም በም​ድር አሕ​ዛብ እጅ አሳ​ል​ፈህ ሰጠ​ሃ​ቸው።


“ነገር ግን ተመ​ል​ሰው ዐመ​ፁ​ብህ፤ ሕግ​ህ​ንም ወደ ኋላ​ቸው ጣሉት፤ ወደ አን​ተም ይመ​ለሱ ዘንድ የመ​ሰ​ከ​ሩ​ባ​ቸ​ውን ነቢ​ያ​ት​ህን ገደሉ፤ እጅ​ግም አስ​ቈ​ጡህ።


የባ​ሪ​ያ​ዎ​ችን የነ​ቢ​ያ​ትን ቃል ትሰሙ ዘንድ በማ​ለዳ ወደ እና​ንተ ብል​ካ​ቸው አል​ሰ​ማ​ች​ሁም።


እነ​ርሱ ግን እን​ዲህ አሉ፥ “የወ​ይ​ኑን ጠጅ አን​ጠ​ጣም፤ አባ​ታ​ችን የሬ​ካብ ልጅ ኢዮ​ና​ዳብ እና​ን​ተና ልጆ​ቻ​ችሁ ለዘ​ለ​ዓ​ለም የወ​ይን ጠጅ አት​ጠጡ ብሎ አዝ​ዞ​ና​ልና።


የሬ​ካብ ልጅ የኢ​ዮ​ና​ዳብ ልጆች አባ​ታ​ቸው ያዘ​ዛ​ቸ​ውን ትእ​ዛዝ ፈጽ​መ​ዋል፤ ይህ ሕዝብ ግን አል​ሰ​ማ​ኝም፤


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios