Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ኤርምያስ 3:6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በን​ጉሡ በኢ​ዮ​ስ​ያስ ዘመን እን​ዲህ አለኝ፥ “ከዳ​ተ​ኛ​ዪቱ እስ​ራ​ኤል ያደ​ረ​ገ​ች​ውን አየ​ህን? ወደ ረዘ​መው ተራራ ሁሉ፥ ወደ ለመ​ለመ ዛፍም ሁሉ በታች ሄደች፤ በዚ​ያም አመ​ነ​ዘ​ረች።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

6 እግዚአብሔር በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን እንዲህ አለኝ፤ “ከዳተኛዪቱ እስራኤል ያደረገችውን አየህን? ከፍ ወዳለው ኰረብታ ሁሉ ወጥታ፣ ወደ ለመለመው ዛፍ ሥር ሁሉ ሄዳ በዚያ አመነዘረች።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

6 ጌታም በንጉሡ በኢዮስያስ ዘመን እንዲህ አለኝ፦ “ከዳተኛይቱ እስራኤል ያደረገችውን አየህን? ወደ ረዘመው ተራራ ሁሉ ከለመለመ ዛፍም ሁሉ በታች ሄደች በዚያም አመነዘረች።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

6 ኢዮስያስ በነገሠበት ዘመን እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፦ “እምነት አጒዳይ የሆነችው እስራኤል ምን እንዳደረገች አይተሃልን? እርስዋ ከእኔ ተለይታ በየከፍተኛው ተራራና በየለመለመው ዛፍ ሥር ጣዖትን በማምለክ ርኲሰትን ፈጽማለች።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

6 እግዚአብሔርም በንጉሡ በኢዮስያስ ዘመን እንዲህ አለኝ፦ ከዳተኛይቱ እስራኤል ያደረገችውን አየህን? ወደ ረዘመው ተራራ ሁሉ ከለመለመ ዛፍም ሁሉ በታች ሄደች በዚያም ጋለሞተች።

Ver Capítulo Copiar




ኤርምያስ 3:6
24 Referencias Cruzadas  

“እኅ​ቷም ሐሊባ ይህን አየች፤ ሆኖም ከእ​ር​ስዋ ይልቅ በፍ​ቅር በመ​ከ​ተ​ልዋ ረከ​ሰች፤ ዝሙ​ቷ​ንም ከእ​ኅቷ ዝሙት ይልቅ አበ​ዛች።


እሰ​ጣ​ቸ​ውም ዘንድ እጄን ወደ አነ​ሣ​ሁ​ላ​ቸው ምድር አገ​ባ​ኋ​ቸው፤ ከፍ ያለ​ውን ኮረ​ብታ ሁሉ፥ ቅጠ​ላ​ማ​ው​ንም ዛፍ ሁሉ አዩ፤ በዚ​ያም ለጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ውን ሠዉ፤ በዚ​ያም የሚ​ያ​ስ​ቈ​ጣ​ኝን፤ ቍር​ባ​ና​ቸ​ውን አቀ​ረቡ፤ በዚ​ያም ደግሞ ጣፋ​ጩን ሽታ​ቸ​ውን አደ​ረጉ፤ በዚ​ያም የመ​ጠጥ ቍር​ባ​ና​ቸ​ውን አፈ​ሰሱ።


በየ​መ​ን​ገዱ ራስ የም​ን​ዝ​ር​ና​ሽን ስፍራ ሠር​ተ​ሻል፤ በየ​አ​ደ​ባ​ባ​ዩም ከፍ ያለ​ውን ቦታ​ሽን አድ​ር​ገ​ሻል። ዋጋ​ዋን እን​ደ​ም​ት​ሰ​በ​ስብ እንደ ጋለ​ሞ​ታም አል​ሆ​ን​ሽም።


ልጆ​ቻ​ቸ​ውም ከለ​መ​ለሙ ዛፎች በታ​ችና በረ​ዘ​ሙት ኮረ​ብ​ቶች ላይ ያሉ​ትን መሠ​ዊ​ያ​ቸ​ው​ንና የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ዳ​ቸ​ውን ያስ​ባሉ።


ነገር ግን በክፉ ልባ​ቸው አሳ​ብና እል​ከ​ኝ​ነት ሄዱ፤ ወደ​ፊ​ትም ሳይ​ሆን ወደ ኋላ​ቸው ሄዱ እንጂ አል​ሰ​ሙ​ኝም ጆሮ​አ​ቸ​ው​ንም አላ​ዘ​ነ​በ​ሉም።


ከዳ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም እስ​ራ​ኤል እን​ዳ​መ​ነ​ዘ​ረች አየሁ፤ የፍ​ች​ዋ​ንም ደብ​ዳቤ በእ​ጅዋ ሰጥቼ ሰደ​ድ​ኋት፤ ጎስ​ቋላ እኅቷ ይሁዳ ግን በዚያ አል​ፈ​ራ​ችም፤ እር​ስ​ዋም ደግሞ ሄዳ አመ​ነ​ዘ​ረች።


ከፍ ባለ​ውና በረ​ዘ​መ​ውም ተራራ ላይ መኝ​ታ​ሽን አደ​ረ​ግሽ፤ በዚ​ያም መሥ​ዋ​ዕ​ት​ሽን ሠዋሽ።


እነ​ር​ሱም ደግሞ ከፍ ባለው ኮረ​ብታ ሁሉ ላይ፥ ቅጠ​ሉም ከለ​መ​ለመ ዛፍ ሁሉ በታች መስ​ገ​ጃ​ዎ​ችን ሠሩ፤ ሐው​ል​ቶ​ች​ንና የማ​ም​ለ​ኪያ አፀ​ዶ​ች​ንም ለራ​ሳ​ቸው አቆሙ።


ኢዮ​ስ​ያ​ስም መን​ገሥ በጀ​መረ ጊዜ የስ​ም​ንት ዓመት ልጅ ነበረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሠላሳ አንድ ዓመት ነገሠ።


በይ​ሁዳ ንጉሥ በአ​ሞጽ ልጅ በኢ​ዮ​ስ​ያስ ዘመን በመ​ን​ግ​ሥቱ በዐ​ሥራ ሦስ​ተ​ኛው ዓመት የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል መጣ​ለት።


የእ​ስ​ራ​ኤል ቤትና የይ​ሁዳ ቤት በእኔ ላይ እጅግ ወን​ጅ​ለ​ዋል” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ቃሌን ይሰሙ ዘንድ እንቢ ወደ አሉ ወደ አባ​ቶ​ቻ​ቸው ኀጢ​አት ተመ​ለሱ፥ ያመ​ል​ኩ​አ​ቸ​ውም ዘንድ እን​ግ​ዶ​ችን አማ​ል​ክት ተከ​ተሉ፤ የእ​ስ​ራ​ኤል ቤትና የይ​ሁዳ ቤት ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ጋር ያደ​ረ​ግ​ሁ​ትን ቃል ኪዳን አፈ​ረሱ።


አንቺ ከዳ​ተኛ ልጅ ሆይ! እስከ መቼ ትቅ​በ​ዘ​በ​ዣ​ለሽ? እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ድር ላይ አዲስ ነገር ፈጥ​ሮ​አ​ልና ሰው ወደ ድኅ​ነት ይመ​ጣል።”


ስማ​ቸ​ውም የታ​ላ​ቂቱ ሐላ የታ​ናሽ እኅ​ቷም ሐሊባ ነበረ፤ እኔም አገ​ባ​ኋ​ቸው፤ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ች​ንም ወለዱ። ስማ​ቸ​ውም ሐላ ሰማ​ርያ ናት፤ ሐሊባ ደግሞ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ናት።


በተ​ራ​ሮ​ችም ራስና በኮ​ረ​ብ​ታ​ዎች ላይ ይሠ​ዋሉ፤ ጥላ​ውም መል​ካም ነውና ከኮ​ም​በ​ልና ከል​ብን፥ ከአ​ሆ​ማም ዛፍ በታች ያር​ዳሉ፤ ስለ​ዚህ ሴቶች ልጆ​ቻ​ችሁ ይሰ​ስ​ናሉ፤ ሙሽ​ሮ​ቻ​ች​ሁም ያመ​ነ​ዝ​ራሉ።


ሕዝ​ቤም ከመ​ኖ​ሪ​ያው ተነ​ሥ​ቶ​አል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በክ​ብሩ ላይ ተቈጣ፤ ከፍ ከፍም አያ​ደ​ር​ገ​ውም።


ሌሎች አማ​ል​ክ​ትን ተከ​ት​ለው አመ​ነ​ዘሩ፤ ሰገ​ዱ​ላ​ቸ​ውም እንጂ፥ መሳ​ፍ​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውን አል​ሰ​ሙም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አስ​ቈ​ጡት፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቃል እን​ዳ​ይ​ሰሙ አባ​ቶ​ቻ​ቸው ይሄ​ዱ​ባት የነ​በ​ረ​ች​ውን መን​ገድ ፈጥ​ነው ተዉ​አት፤ እን​ዲ​ሁም አላ​ደ​ረ​ጉም።


እነ​ርሱ በክፉ መከ​ራና በጭ​ን​ቀት ተሠ​ቃዩ፥ እያ​ነ​ሱም ሄዱ፤


እና​ንተ የኃ​ጥ​ኣን ልጆች፥ የዘ​ማ​ው​ያ​ንና የጋ​ለ​ሞ​ታ​ዪቱ ዘር፥ ወደ​ዚህ ቅረቡ።


“ስለ​ዚህ ዘማ ሆይ! የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስሚ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios