Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ኤርምያስ 27:15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

15 እኔ አል​ላ​ክ​ኋ​ቸ​ው​ምና፤ ነገር ግን እኔ እን​ዳ​ሳ​ድ​ዳ​ችሁ፥ እና​ን​ተና ትን​ቢት የሚ​ና​ገ​ሩ​ላ​ችሁ ነቢ​ያ​ትም እን​ድ​ት​ጠፉ በስሜ ሐሰ​ተኛ ትን​ቢ​ትን ይና​ገ​ራሉ፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።”

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

15 ‘እኔ አልላክኋቸውም’ ይላል እግዚአብሔር ‘የሐሰት ትንቢት በስሜ ይናገራሉ፤ ስለዚህ እናንተንና ትንቢት የሚናገሩላችሁን ነቢያት አሳድዳለሁ፤ እናንተም ትጠፋላችሁ።’ ”

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

15 እኔ አልላክኋቸውምና፤ ነገር ግን እኔ እንዳሳድዳችሁ፥ እናንተና ትንቢት የሚነግሩአችሁ ነቢያትም እንድትጠፉ፥ በስሜ ሐሰተኛ ትንቢትን ይናገራሉ፥ ይላል ጌታ።”

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

15 እርሱ ያልላካቸው መሆኑንና እነርሱ በስሙ የሚነግሩአችሁ ሁሉ ውሸት መሆኑን እግዚአብሔር ራሱ ነግሮአችኋል። ስለዚህ እርሱ ያሳድዳችኋል፤ እናንተና ይህን ውሸት የሚነግሩአችሁ ነቢያት ሁሉ ትጠፋላችሁ።”

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

15 እኔ አልላክኋቸውምና፥ ነገር ግን እኔ እንዳሳድዳችሁ፥ እናንተና ትንቢት የሚናገሩላችሁ ነቢያትም እንድትጠፉ በስሜ ሐሰተኛ ትንቢትን ይናገራሉ፥ ይላል እግዚአብሔር።

Ver Capítulo Copiar




ኤርምያስ 27:15
27 Referencias Cruzadas  

እር​ሱም ይህን ሲና​ገር ንጉሡ አሜ​ስ​ያስ፥ “በውኑ የን​ጉሡ አማ​ካሪ ልት​ሆን ሹሜ​ሃ​ለ​ሁን? ቅጣት እን​ዳ​ያ​ገ​ኝህ ተጠ​ን​ቀቅ” አለው። ነቢ​ዩም፥ “ይህን አድ​ር​ገ​ሃ​ልና፥ ምክ​ሬ​ንም አል​ሰ​ማ​ህ​ምና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሊያ​ጠ​ፋህ እን​ዳ​ሰበ አወ​ቅሁ” ብሎ ዝም አለ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ አለኝ፥ “ነቢ​ያቱ በስሜ የሐ​ሰት ትን​ቢት ይና​ገ​ራሉ፤ አላ​ክ​ኋ​ቸ​ውም፤ አላ​ዘ​ዝ​ኋ​ቸ​ውም፤ አል​ተ​ና​ገ​ር​ኋ​ቸ​ውም፤ የሐ​ሰ​ቱን ራእይ፥ ምዋ​ር​ት​ንም፥ ከን​ቱ​ንም ነገር፥ በል​ባ​ቸ​ውም የፈ​ጠ​ሩ​ትን ይተ​ነ​ብ​ዩ​ላ​ች​ኋል።”


አን​ተም ጳስ​ኮር ሆይ! በቤ​ት​ህም የሚ​ኖ​ሩት ሁሉ ተማ​ር​ካ​ችሁ ትሄ​ዳ​ላ​ችሁ፤ አን​ተም በሐ​ሰት ትን​ቢት የተ​ና​ገ​ር​ህ​ላ​ቸው ወዳ​ጆ​ችህ ሁሉ ወደ ባቢ​ሎን ትገ​ባ​ላ​ችሁ፤ በዚ​ያም ትሞ​ታ​ላ​ችሁ፤ በዚ​ያም ትቀ​በ​ራ​ላ​ችሁ።”


ስለ​ዚህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “እነሆ ከኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ነቢ​ያት ዘንድ ርኵ​ሰት በም​ድር ሁሉ ላይ ወጥ​ቶ​አ​ልና ሕማ​ምን አበ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ መራራ ውኃ​ንም አጠ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ።”


“እኔ ሳል​ል​ካ​ቸው እነ​ዚህ ነቢ​ያት ሮጡ፤ እኔም ሳል​ነ​ግ​ራ​ቸው ትን​ቢ​ትን ተና​ገሩ።


ሕል​ምን አለ​ምን እያሉ በስሜ ሐሰ​ተኛ ትን​ቢት የሚ​ና​ገ​ሩ​ትን የነ​ቢ​ያ​ትን ነገር ሰም​ቻ​ለሁ።


ከም​ድ​ራ​ችሁ እን​ዲ​ያ​ር​ቁ​አ​ችሁ፥ እኔም እን​ዳ​ሳ​ድ​ዳ​ችሁ፥ እና​ን​ተም እን​ድ​ት​ጠፉ ሐሰ​ተኛ ትን​ቢ​ትን ይና​ገ​ሩ​ላ​ች​ኋ​ልና።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም አም​ላክ የሠ​ራ​ዊት ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላ​ልና፥ “በመ​ካ​ከ​ላ​ችሁ ያሉት የሐ​ሰት ነቢ​ያ​ቶ​ቻ​ች​ሁና ምዋ​ር​ተ​ኞ​ቻ​ችሁ አያ​ታ​ል​ሉ​አ​ችሁ፤ ሕልም አላ​ሚ​ዎች አለ​ም​ን​ላ​ችሁ የሚ​ሉ​አ​ች​ሁን አት​ስሙ፥


በስሜ ሐሰ​ተኛ ትን​ቢ​ትን ይና​ገ​ሩ​ላ​ች​ኋ​ልና፤ እኔም አል​ላ​ክ​ኋ​ቸ​ውም፥” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


እነሆ በይ​ሁዳ ቤት የቀ​ሩ​ትን ሴቶች ሁሉ ወደ ባቢ​ሎን ንጉሥ አለ​ቆች ያወ​ጣሉ፤ እነ​ዚ​ያም ሴቶች፦ ባለ​ሟ​ሎ​ችህ አታ​ል​ለ​ው​ሃል፤ አሸ​ን​ፈ​ው​ህ​ማል፤ እግ​ሮ​ችህ ግን አሁን በጭቃ ውስጥ ከገቡ እነ​ርሱ ከአ​ንተ ወደ ኋላ ተመ​ል​ሰ​ዋል ይላሉ።


ተዉአቸው፤ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ፤” አለ።


ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፤ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ።


አውሬውም ተያዘ፤ በእርሱም ፊት ተአምራትን እያደረገ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትን ለምስሉም የሰገዱትን ያሳተ ሐሰተኛው ነቢይ ከእርሱ ጋር ተያዘ፤ ሁለቱም በሕይወት ሳሉ በዲን ወደሚቃጠል ወደ እሳት ባሕር ተጣሉ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos