Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ዕብራውያን 10:30 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

30 “እኔ እበ​ቀ​ላ​ለሁ፤ እኔም ብድ​ራ​ትን እመ​ል​ሳ​ለሁ፥” ያለ​ውን እና​ው​ቀ​ዋ​ለ​ንና፤ ዳግ​መ​ኛም “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሕ​ዝቡ ላይ ይፈ​ር​ዳል።”

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

30 “በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ” ያለውን እናውቀዋለንና፤ ደግሞም፣ “ጌታ በሕዝቡ ላይ ይፈርዳል” ይላል።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

30 “በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ፤” ያለውን እናውቃለን፤ ደግሞም “ጌታ በሕዝቡ ይፈርዳል።”

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

30 “በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ተገቢ ዋጋን እከፍላለሁ” ያለው ማን መሆኑን እናውቃለን፤ እንዲሁም “እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ ይፈርዳል” ይላል ጌታ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

30 በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ ያለውን እናውቃለንና፤ ደግሞም፦ ጌታ በሕዝቡ ይፈርዳል።

Ver Capítulo Copiar




ዕብራውያን 10:30
18 Referencias Cruzadas  

ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን፥ ራሳ​ችሁ አት​በ​ቀሉ፤ ቍጣን አሳ​ል​ፏት፥ “እኔ እበ​ቀ​ላ​ለሁ፤ እኔ ብድ​ራ​ትን እከ​ፍ​ላ​ለሁ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር” ተብሎ ተጽ​ፎ​አ​ልና።


እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው፣ እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው፣ እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል።


አን​ተን ብቻ በደ​ልሁ፥ በፊ​ት​ህም ክፋ​ትን አደ​ረ​ግሁ፥ በነ​ገ​ርህ ትጸ​ድቅ ዘንድ በፍ​ር​ድ​ህም ታሸ​ንፍ ዘንድ።


መል​ካም ቢሆን፥ ክፉም ቢሆን በሥ​ጋ​ችን እንደ ሠራ​ነው ዋጋ​ች​ንን እን​ቀ​በል ዘንድ፥ ሁላ​ችን በክ​ር​ስ​ቶስ የፍ​ርድ ዙፋን ፊት እን​ቆ​ማ​ለ​ንና።


እስ​ራ​ኤ​ልን በመ​ካ​ከሉ ያሳ​ለፈ፤ ምሕ​ረቱ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና፤


አንተ ሥራ​ህን ታሳ​ምር ዘንድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​እ​ክ​ተ​ኞች ናቸ​ውና። ክፉ ብታ​ደ​ርግ ግን ፍራ፤ ሰይፍ የታ​ጠ​ቁም ለከ​ንቱ አይ​ደ​ለም፤ ክፉ አድ​ራ​ጊ​ዎ​ችን ለመ​ቅ​ጣት የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ጋ​ዮች ናቸ​ውና።


የተ​ወ​ደ​ደ​ች​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ዓመት የተ​መ​ረ​ጠች ብዬ እጠ​ራት ዘንድ፥ አም​ላ​ካ​ች​ንም የሚ​በ​ቀ​ል​በ​ትን ቀን እና​ገር ዘንድ፥ የሚ​ያ​ለ​ቅ​ሱ​ት​ንም ሁሉ አጽ​ናና ዘንድ፥


አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከፍ ከፍ አለ፥ በተ​ቀ​ደ​ሰው ተራራ ይሰ​ግ​ዱ​ለ​ታል፤ አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቅዱስ ነውና።


የእ​ስ​ራ​ኤል ቤት ሆይ! ስለ​ዚህ እንደ መን​ገዱ በየ​ሰዉ ሁሉ እፈ​ር​ድ​ባ​ች​ኋ​ለሁ፥ ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ ንስሓ ግቡ፤ ኀጢ​አ​ትም ዕን​ቅ​ፋት እን​ዳ​ይ​ሆ​ን​ባ​ችሁ ከኀ​ጢ​አ​ታ​ችሁ ሁሉ ተመ​ለሱ።


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “እና​ን​ተም መን​ጋዬ ሆይ! እነሆ በበ​ግና በበግ መካ​ከል፥ በአ​ውራ በግና በአ​ውራ ፍየ​ልም መካ​ከል እፈ​ር​ዳ​ለሁ።


የም​በ​ቀ​ል​በት ቀን ደር​ሶ​ባ​ቸ​ዋ​ልና፥ የም​ቤ​ዥ​በ​ትም ዐመት ደር​ሶ​አ​ልና።


ጽድ​ቅ​ንም እንደ ጥሩር ለበሰ፤ በራ​ሱም ላይ የማ​ዳ​ንን ራስ ቍር አደ​ረገ፤ የበ​ቀ​ል​ንም ልብስ ለበሰ።


ኑ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ደስ ይበ​ለን፤ ለአ​ም​ላ​ካ​ች​ንና ለመ​ድ​ኀ​ኒ​ታ​ች​ንም እልል እን​በል፥


አት​በ​ቀል፤ በሕ​ዝ​ብ​ህም ልጆች ቂም አት​ያዝ፤ ነገር ግን ባል​ን​ጀ​ራ​ህን እንደ ራስህ ውደድ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ክህ ነኝና።


አሁ​ንም ጌታዬ ሆይ! ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! በሕ​ያው ነፍ​ስህ እም​ላ​ለሁ! ወደ ንጹሕ ደም እን​ዳ​ት​ገ​ባና፥ እጅ​ህን እን​ድ​ታ​ድን የከ​ለ​ከ​ለህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፤ አሁ​ንም ጠላ​ቶ​ች​ህና በጌ​ታዬ ላይ ክፉ የሚሹ ሁሉ እንደ ናባል ይሁኑ።


ደግ​ሞም ዳዊት አለው፥ “ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ካል​ገ​ደ​ለው፥ ወይም ቀኑ ደርሶ ካል​ሞተ፥ ወይም ወደ ጦር​ነት ወርዶ ካል​ሞተ እኔ አል​ገ​ድ​ለ​ውም።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios