Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዘፍጥረት 33:13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

13 እር​ሱም አለው፥ “ጌታዬ ሆይ፥ ልጆቹ ደካ​ሞች እንደ ሆኑ ታው​ቃ​ለህ፤ በጎ​ችና ላሞ​ችም ግል​ገ​ሎ​ቻ​ቸ​ውን ያጠ​ባሉ፤ ሰዎ​ችም በአ​ንድ ወይም በሁ​ለት ቀን በች​ኮላ የነ​ዱ​አ​ቸው እንደ ሆነ ከብ​ቶቹ ሁሉ ይሞ​ታሉ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

13 ያዕቆብ ግን እንዲህ አለው፤ “ጌታዬ፣ እንደምታየው ልጆቹ ይህን ያህል የጠኑ አይደሉም፣ ለሚያጠቡት በጎችና ጥገቶች እንክብካቤ ማድረግ አለብኝ፤ እንስሳቱ ለአንዲት ቀን እንኳ በጥድፊያ ቢነዱ በሙሉ ያልቃሉ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

13 እርሱም አለው፥ “ጌታዬ ሆይ፥ ልጆቹ ደካሞች እንደ ሆኑ ታውቃለህ፥ በጎችና ላሞችም ግልገሎቻቸውን ያጠባሉ መጠንቀቅ ይኖርብኛል፤ ሰዎችም አንድ ቀን በችኮላ የነዱአቸው እንደሆነ እንሰሶቹ ሁሉ ይሞታሉ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

13 ያዕቆብም እንዲህ አለ፤ “ልጆቹ ደካሞች እንደ ሆኑ ጌታዬ ታውቃለህ፤ ለሚያጠቡት እንስሶች፥ ለግልገሎቻቸውና ለእንቦሶቻቸው መጠንቀቅ ይኖርብኛል፤ ለአንድ ቀን እንኳ በጥድፊያ ቢነዱ እንስሶቹ በሙሉ ያልቃሉ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

13 እርሱም አለው፦ ጌታዬ ሆይ ልጆቹ ደካሞች እንደ ሆኑ ታውቃለህ በጎችና ላሞችም ግልገሎቻቸውን ያጠባሉ ሰዎችም አንድ ቀን በችኮላ የነዱአቸው እንደ ሆን ከብቶቹ ሁሉ ይሞታሉ።

Ver Capítulo Copiar




ዘፍጥረት 33:13
10 Referencias Cruzadas  

እር​ሱም፥ “ተነ​ሣና ወደ ፊት እን​ሂድ” አለው።


ጌታዬ ከአ​ገ​ል​ጋዩ ፊት ቀድሞ ይለፍ፤ እኛም እንደ ቻልን እን​ሄ​ዳ​ለን፤ በጎ​ዳ​ናም እን​ው​ላ​ለን፤ ወደ ጌታ​ችን ወደ ሴይር እስ​ክ​ን​ደ​ር​ስም በሕ​ፃ​ናቱ ርምጃ መጠን እን​ሄ​ዳ​ለን” አለው።


ዳዊ​ትም፥ “ልጄ ሰሎ​ሞን ታና​ሽና ለጋ ብላ​ቴና ነው፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ሠ​ራው ቤት እጅግ ማለ​ፊ​ያና በሀ​ገሩ ሁሉ ስሙና ክብሩ እን​ዲ​ጠራ ይሆን ዘንድ ይገ​ባል፤ ስለ​ዚህ አዘ​ጋ​ጅ​ለ​ታ​ለሁ” አለ። ዳዊ​ትም ሳይ​ሞት አስ​ቀ​ድሞ ብዙ አዘ​ጋጀ።


ጻድቅ ሰው ለእንስሳው ነፍስ ይራራል፤ የኃጥኣን ምሕረት ግን አለመመጽወት ነው።


መን​ጋ​ውን እንደ እረኛ ያሰ​ማ​ራል፤ ጠቦ​ቶ​ቹን በክ​ንዱ ሰብ​ስቦ በብ​ብቱ ይሸ​ከ​ማል፤ የሚ​ያ​ጠ​ቡ​ት​ንም በቀ​ስታ ይመ​ራል።


ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም እን​ዲሁ አደ​ረጉ፤ የሚ​ያ​ጠ​ቡ​ትን ሁለ​ቱን ላሞች ወሰዱ፤ በሰ​ረ​ገ​ላ​ውም ጠመ​ዱ​አ​ቸው፤ እን​ቦ​ሶ​ቻ​ቸ​ው​ንም በቤት ዘጉ​ባ​ቸው፤


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos