Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ዘፍጥረት 16:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

3 አብ​ራ​ምም በከ​ነ​ዓን ምድር ዐሥር ዓመት ከተ​ቀ​መጠ በኋላ፥ የአ​ብ​ራም ሚስት ሦራ ግብ​ፃ​ዊት አገ​ል​ጋ​ይ​ዋን አጋ​ርን ወስዳ ለአ​ብ​ራም ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ ሰጠ​ችው።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

3 አብራም በከነዓን ምድር ዐሥር ዓመት ከኖረ በኋላ ሚስቱ ሦራ ግብጻዊት አገልጋይዋን አጋርን ሚስት እንድትሆነው ለባሏ ሰጠችው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

3 አብራምም የሦራን ቃል ሰማ። አብራምም በከነዓን ምድር ዐሥር ዓመት ከተቀመጠ በኋላ፥ የአብራም ሚስት ሦራ ግብፃዊት ባርያዋን አጋርን ወስዳ ለባልዋ ለአብራም ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠችው።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

3 ስለዚህ ሣራይ ግብጻዊት የሆነች አገልጋይዋን አጋርን ለአብራም ሚስት እንድትሆነው ሰጠችው። ይህም የሆነው አብራም በከነዓን ዐሥር ዓመት ከኖረ በኋላ ነው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

3 አብራምም የሦራን ቃል ሰማ። አብራምም በከነዓን ምድር አሥር ዓመት ከተቀመጠ በኍላ፤ የአብራም ሚስት ሦራ ግብፃዊት ባሪያዋን አጋርን ወስዳ ለባልዋ ለአብራም ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠችው።

Ver Capítulo Copiar




ዘፍጥረት 16:3
15 Referencias Cruzadas  

ሦራም አብ​ራ​ምን፥ “ከአ​ንተ የተ​ነሣ እገ​ፋ​ለሁ፤ እኔ አገ​ል​ጋ​ዬን በብ​ብ​ትህ ሰጠ​ሁህ፤ እንደ ፀነ​ሰ​ችም ባየች ጊዜ እኔን ማክ​በ​ርን ተወች፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእ​ኔና በአ​ንተ መካ​ከል ይፍ​ረድ” አለ​ችው።


አጋ​ርም በዐ​ረብ ሀገር ያለች ደብረ ሲና ናት፤ ከዛ​ሬ​ዪቱ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ጋር ትነ​ጻ​ጸ​ራ​ለች፤ ከል​ጆ​ችዋ ጋርም ትገ​ዛ​ለች።


ለእ​ር​ሱም ሰባት መቶ ሚስ​ቶ​ችና ሦስት መቶ ቁባ​ቶች ነበ​ሩት።


ዳዊ​ትም ከኬ​ብ​ሮን ከመጣ በኋላ እንደ ገና ቁባ​ቶ​ቹ​ንና ሚስ​ቶ​ቹን ከኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ወሰደ፤ ለዳ​ዊ​ትም ደግሞ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆች ተወ​ለ​ዱ​ለት።


የያ​ዕ​ቆ​ብም ልጆች ዐሥራ ሁለት ናቸው፤


በዚ​ያ​ችም ሌሊት ተነሣ፥ ሁለ​ቱን ሚስ​ቶ​ቹ​ንና ሁለ​ቱን ዕቁ​ባ​ቶ​ቹን ዐሥራ አን​ዱ​ንም ልጆ​ቹን ይዞ የያ​ቦ​ቅን ወንዝ ተሻ​ገረ።


ልያም መው​ለ​ድን እን​ዳ​ቆ​መች በአ​የች ጊዜ አገ​ል​ጋ​ይ​ዋን ዘለ​ፋን ወሰ​ደች፤ ሚስት ትሆ​ነ​ውም ዘንድ ለያ​ዕ​ቆብ ሰጠ​ችው፤ ያዕ​ቆ​ብም ወደ እር​ስዋ ገባ።


አገ​ል​ጋ​ይ​ዋን ባላ​ንም ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ ለእ​ርሱ ሰጠ​ችው፤ ያዕ​ቆ​ብም ወደ እር​ስዋ ገባ።


ዔሳው ወደ ይስ​ማ​ኤል ሄደ፤ ቤሴ​ሞ​ት​ንም በፊት ካሉ ሚስ​ቶቹ ጋር ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ ወሰ​ዳት፤ እር​ስ​ዋም የና​ኮር ወን​ድም የአ​ብ​ር​ሃም ልጅ የሆ​ነው የይ​ስ​ማ​ኤል ልጅና የና​ቡ​ዓት እኅት ናት።


አብ​ር​ሃ​ምም ለቁ​ባ​ቶቹ ልጆች ሀብ​ትን ሰጣ​ቸው፤ እር​ሱም ገና በሕ​ይ​ወቱ ሳለ ከልጁ ከይ​ስ​ሐቅ ለይቶ ወደ ምሥ​ራቅ ሀገር ሰደ​ዳ​ቸው።


አብ​ራ​ምም ወደ አጋር ገባ፤ ፀነ​ሰ​ችም፤ እንደ ፀነ​ሰ​ችም ባየች ጊዜ እመ​ቤ​ቷን ማክ​በ​ር​ዋን ተወች።


አጋር ይስ​ማ​ኤ​ልን በወ​ለ​ደ​ች​ለት ጊዜ አብ​ራም የሰ​ማ​ንያ አም​ስት ዓመት ሰው ነበረ።


በፋ​ራን ምድረ በዳም ተቀ​መጠ፤ እና​ቱም ከም​ድረ ግብፅ ሚስት ወሰ​ደ​ች​ለት።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios