Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ዘፍጥረት 1:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለ፥ “በም​ድር ላይ ያበሩ ዘንድ፥ በቀ​ንና በሌ​ሊ​ትም ይለዩ ዘንድ ብር​ሃ​ናት በሰ​ማይ ጠፈር ይሁኑ፤ ለም​ል​ክ​ቶች፥ ለዘ​መ​ናት፥ ለዕ​ለ​ታት፥ ለዓ​መ​ታ​ትም ይሁኑ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

14 ከዚያም እግዚአብሔር፣ “ቀኑን ከሌሊት እንዲለዩ፣ የዓመት ወቅቶች፣ ቀናትና ዓመታት የሚጀምሩበትንም እንዲያመለክቱ፣

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

14 እግዚአብሔርም አለ፦ “ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፥ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፥

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

14 ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር እንዲህ አለ፦ “ቀንን ከሌሊት ለመለየት ልዩ ልዩ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ላይ ይሁኑ፤ ለዕለታት፥ ለክፍላተ ዓመትና ለዓመታት መለያ ምልክት ይሁኑ፤

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

14 እግዚአብሔርም አለ፤ ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፤

Ver Capítulo Copiar




ዘፍጥረት 1:14
43 Referencias Cruzadas  

ወደ ሰማይ አት​መ​ል​ከት፤ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከሰ​ማይ ሁሉ በታች ላሉት አሕ​ዛብ ሁሉ የሰ​ጣ​ቸ​ውን ፀሐ​ይ​ንና ጨረ​ቃን፥ ከዋ​ክ​ብ​ት​ንና የሰ​ማ​ይን ሠራ​ዊት ሁሉ አይ​ተህ፥ ሰግ​ደ​ህ​ላ​ቸው፥ አም​ል​ከ​ሃ​ቸ​ውም እን​ዳ​ት​ስት ተጠ​ን​ቀቅ።


ስሙ የሠ​ራ​ዊት ጌታ የሚ​ባል፥ ፀሐ​ይን በቀን፥ ጨረ​ቃ​ንና ከዋ​ክ​ብ​ት​ንም በሌ​ሊት ብር​ሃን አድ​ርጎ የሚ​ሰጥ፥ እን​ዲ​ተ​ም​ሙም የባ​ሕ​ርን ሞገ​ዶች የሚ​ያ​ና​ውጥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦


ፀሐ​ይና ጨረቃ ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ታል፤ ከዋ​ክ​ብ​ትና ብር​ሃን ሁሉ ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ታል።


ለዘ​ለ​ዓ​ለም አቆ​ማ​ቸው፤ ትእ​ዛ​ዝን ሰጣ​ቸው፥ አላ​ለ​ፉ​ምም።


ሁሉን የሚ​ሠ​ራና የሚ​ያ​ቅ​ናና፥ ብር​ሃ​ኑን ወደ መስዕ የሚ​መ​ል​ሰው፥ ቀኑን እንደ ሌሊት የሚ​ያ​ጨ​ል​መው፥ የባ​ሕ​ሩ​ንም ውኃ ጠርቶ በም​ድር ፊት የሚ​ያ​ፈ​ስ​ሰው ስሙ ሁሉን የሚ​ችል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው።


ፀሐ​ይና ጨረቃ ይጨ​ል​ማሉ፤ ከዋ​ክ​ብ​ትም ብር​ሃ​ና​ቸ​ውን ይሰ​ው​ራሉ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “የአ​ሕ​ዛ​ብን መን​ገድ አት​ማሩ፤ ከሰ​ማይ ምል​ክ​ትም አት​ፍሩ፤ አሕ​ዛብ ከእ​ነ​ርሱ የተ​ነሣ ይፈ​ራ​ሉና።


ለድ​ሆ​ችና ለድሃ አደ​ጎች ፍረዱ፤ ለተ​ገ​ፋ​ውና ለም​ስ​ኪኑ ጽድ​ቅን አድ​ርጉ፤


በም​ድር ዘመን ሁሉ መዝ​ራ​ትና ማጨድ፥ ብር​ድና ሙቀት፥ በጋና ክረ​ምት፥ ቀንና ሌሊት አያ​ቋ​ር​ጡም።”


ዐይ​ና​ች​ሁን ወደ ሰማይ አን​ሥ​ታ​ችሁ ተመ​ል​ከቱ፤ ይህን ሁሉ የፈ​ጠረ ማን ነው? ከዋ​ክ​ብ​ት​ንም በሙሉ የሚ​ቈ​ጥ​ራ​ቸው እርሱ ነው፤ በየ​ጊ​ዜ​ያ​ቸው ያመ​ጣ​ቸ​ዋል፤ ሁሉ​ንም በየ​ስ​ማ​ቸው ይጠ​ራ​ቸ​ዋል፤ በክ​ብሩ ብዛ​ትና በች​ሎቱ ብር​ታት አን​ድስ እንኳ አይ​ታ​ጣ​ውም።


“ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፤ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፤


በዚ​ያም ቀን ፀሐይ በቀ​ትር ይገ​ባል፥ ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ ብር​ሃ​ንም በም​ድር ላይ በቀን ይጨ​ል​ማል።


ምድ​ሪ​ቱም ከፊ​ታ​ቸው ትደ​ነ​ግ​ጣ​ለች፤ ሰማ​ይም ይን​ቀ​ጠ​ቀ​ጣል፤ ፀሐ​ይና ጨረ​ቃም ይጨ​ል​ማሉ፤ ከዋ​ክ​ብ​ትም ብር​ሃ​ና​ቸ​ውን ይሰ​ው​ራሉ።


“እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ቀንና ሌሊት በወ​ራ​ታ​ቸው እን​ዳ​ይ​ሆኑ የቀን ቃል ኪዳ​ኔ​ንና የሌ​ሊት ቃል ኪዳ​ኔን ማፍ​ረስ ብት​ችሉ፥


ስድስተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ አየሁ፤ ታላቅም የምድር መናወጥ ሆነ፤ ፀሐይም እንደ ማቅ ጠጕር ጥቁር ሆነ፤ ጨረቃም በሞላው እንደ ደም ሆነ፤


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “በው​ስ​ጠ​ኛው አደ​ባ​ባይ ወደ ምሥ​ራቅ የሚ​መ​ለ​ከ​ተው በር ሥራ በሚ​ሠ​ራ​በት በስ​ድ​ስቱ ቀን ተዘ​ግቶ ይቈይ፤ ነገር ግን በሰ​ን​በት ቀን ይከ​ፈት፤ በመ​ባቻ ቀንም ይከ​ፈት።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የቀ​ንና የሌ​ሊት ቃል ኪዳ​ኔን የሰ​ማ​ይ​ንና የም​ድ​ር​ንም ሥር​ዐት ያላ​ጸ​ናሁ እንደ ሆነ፥


እነሆ፥ ጨረቃ እንኳ ይሰ​ወ​ራል፤ አያ​በ​ራ​ምም፤ ከዋ​ክ​ብ​ትም በፊቱ ንጹ​ሓን አይ​ደ​ሉም።


ቀስ​ቴን በደ​መና አኖ​ራ​ለሁ፤ የቃል ኪዳ​ኔም ምል​ክት በእ​ኔና በም​ድር መካ​ከል ይሆ​ናል።


አራተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ የፀሐይ ሲሶና የጨረቃ ሲሶ የከዋክብትም ሲሶ ተመታ፤ የእነዚህ ሲሶ ይጨልም ዘንድ፥ የቀንም ሲሶው እንዳያበራ፥ እንዲሁም የሌሊት።


ፀሐ​ዩም በጨ​ለመ ጊዜ የቤተ መቅ​ደሱ መጋ​ረጃ ከላይ እስከ ታች ከመ​ካ​ከሉ ተቀ​ደደ።


“በነዚያ ቀኖች ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፤


በመ​ባ​ቻም ቀን ነውር የሌ​ለ​በ​ትን አንድ ወይ​ፈን፥ ነውር የሌ​ለ​ባ​ቸ​ው​ንም ስድ​ስት ጠቦ​ቶ​ችና አንድ አውራ በግ ያቅ​ርብ፤


ለሌ​ቦች ዕረ​ፍ​ትን የሚ​ሰጥ እን​ዳለ የሚ​መ​ስ​ለው አይ​ኑር። የክ​ፋ​ቱስ ወጥ​መድ የማ​ይ​መ​ጣ​በት ማን ነው?


የዚያ ሌሊት ኮከ​ቦች ይጨ​ልሙ፤ ሌሊ​ቱም በጨ​ለማ ይኑር፤ ወደ ብር​ሃ​ንም አይ​ምጣ፤ የን​ጋት ኮከ​ብም ሲወጣ አይይ፤


የጥልቁንም ጕድጓድ ከፈተው፤ ጢስም ከታላቅ እቶን እንደሚወጣ ጢስ ሆኖ ከጕድጓዱ ወጣ፤ ፀሐይና አየርም በጕድጓዱ ጢስ ጨለሙ።


ማታም ሆነ፤ ጥዋ​ትም ሆነ። ሦስ​ተ​ኛም ቀን ሆነ።


በም​ድር ላይ ያበሩ ዘንድ፥ በሰ​ማይ ጠፈር ለማ​ብ​ራት ይሁኑ፤” እን​ዲ​ሁም ሆነ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በተ​ቀ​ደሱ ቦታ​ዎች አመ​ስ​ግ​ኑት፤ በኀ​ይሉ ጽናት አመ​ስ​ግ​ኑት።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios