Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ገላትያ 5:10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

10 እኔ ሌላ እን​ዳ​ታ​ስቡ በጌ​ታ​ችን በኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶስ አም​ኛ​ችሁ ነበር፤ የሚ​ያ​ው​ካ​ችሁ ግን የሆ​ነው ቢሆን ፍዳ​ውን ይሸ​ከ​ማል።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

10 የተለየ ሐሳብ እንደማይኖራችሁ በጌታ እታመናለሁ። ግራ የሚያጋባችሁ ማንም ይሁን ማን፣ ፍርዱን ይቀበላል።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

10 ሌላ ነገር እንደማታስቡ ስለ እናንተ በጌታ እተማመናለሁ፤ የሚያውካችሁ፥ ማንም ቢሆን ፍርዱን ይቀበላል።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

10 ነገር ግን ከዚህ የተለየ ሌላ ሐሳብ እንደማይኖራችሁ እርግጠኛ ሆኜ በጌታ እተማመናለሁ፤ ማንም ግራ የሚያጋባችሁ ቢኖር ቅጣቱን ይቀበላል።

Ver Capítulo Copiar




ገላትያ 5:10
28 Referencias Cruzadas  

የሚ​ያ​ው​ኩ​አ​ች​ሁም ሊለዩ ይገ​ባል።


ፍጹ​ማን የሆ​ና​ችሁ ሁላ​ችሁ ይህን አስቡ፤ ሌላ የም​ታ​ስ​ቡት ቢኖ​ርም፥ እር​ሱን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይገ​ል​ጥ​ላ​ች​ኋል።


እርሱ ግን ሌላ አይ​ደ​ለም፤ የሚ​ያ​ው​ኳ​ችሁ ከክ​ር​ስ​ቶ​ስም ወን​ጌል ሊያ​ጣ​ምሙ የሚ​ወዱ አሉ እንጂ።


የእኔ ደስታ የሁ​ላ​ችሁ እንደ ሆነ በሁ​ላ​ችሁ አም​ኛ​ለ​ሁና በመ​ጣሁ ጊዜ ደስ ሊያ​ሰ​ኙኝ ከሚ​ገ​ባ​ቸው ኀዘን እን​ዳ​ያ​ገ​ኘኝ ይህን ጻፍ​ሁ​ላ​ችሁ።


ከእነዚያም እንዳይሳደቡ ይማሩ ዘንድ ለሰይጣን አሳልፌ የሰጠኋቸው ሄሜኔዎስና እስክንድሮስ ናቸው።


እን​ግ​ዲህ ወዲ​ህስ የሚ​ያ​ደ​ክ​መኝ አይ​ኑር፤ እኔ የኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶ​ስን መከራ በሥ​ጋዬ እሸ​ከ​ማ​ለሁ።


እነ​ዚ​ያማ ይቀ​ኑ​ባ​ች​ኋል፤ ነገር ግን በእ​ነ​ርሱ ላይ እን​ድ​ት​ቀኑ ሊዘ​ጉ​አ​ችሁ ይወ​ዳሉ እንጂ ለመ​ል​ካም አይ​ደ​ለም።


እና​ንተ ሰነ​ፎች የገ​ላ​ትያ ሰዎች ሆይ፥ ለዐ​ይን በሚ​ታ​የው እው​ነት እን​ዳ​ታ​ምኑ ማን አታ​ለ​ላ​ችሁ? እር​ሱም እን​ዲ​ሰ​ቀል አስ​ቀ​ድሞ የተ​ጻ​ፈ​ለት ኢየ​ሱስ ክር​ስ​ቶስ ነው።


አለ​ቆች የመ​ሰ​ሉት ግን ቀድሞ እነ​ርሱ እን​ዴት እንደ ነበሩ ልና​ገር አያ​ገ​ደ​ኝም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሰው ፊት አያ​ዳ​ላ​ምና፤ አለ​ቆች የመ​ሰ​ሉ​ትም ከራ​ሳ​ቸው ምንም ነገር የጨ​መ​ሩ​ልኝ የለ​ምና።


ይኸ​ውም ባሪ​ያ​ዎች ያደ​ር​ጉን ዘንድ በኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶስ ያገ​ኘ​ና​ትን ነጻ​ነት ሊሰ​ልሉ በስ​ውር ወደ እኛ የገቡ ሐሰ​ተ​ኞች መም​ህ​ራ​ንን ደስ አይ​በ​ላ​ቸው ብዬ ነው።


እና​ንተ ትእ​ዛ​ዝን በፈ​ጸ​ማ​ችሁ ጊዜ የማ​ይ​ገ​ዛ​ውን ሁሉ እኛ ልን​በ​ቀ​ለው ዝግ​ጁ​ዎች ነን።


ሥጋ​ውን ጎድቶ ጌታ​ችን ኢየ​ሱስ ክር​ስ​ቶስ በሚ​መ​ጣ​በት ቀን ነፍሱ ትድን ዘንድ እን​ዲህ ያለ​ውን ሰው ለሰ​ይ​ጣን አሳ​ል​ፋ​ችሁ ስጡት።


ያላ​ዘ​ዝ​ና​ቸው ሰዎች ከእኛ ወጥ​ተው፦ ‘ትገ​ዘሩ ዘን​ድና የኦ​ሪ​ት​ንም ሕግ ትጠ​ብቁ ዘንድ ይገ​ባ​ች​ኋል’ ብለው በነ​ገር እንደ አወ​ኩ​አ​ች​ሁና ልባ​ች​ሁን እንደ አና​ወ​ጡት ሰም​ተ​ናል።


ከምልህ ይልቅ አብልጠህ እንድታደርግ አውቄ እንድትታዘዝም ታምኜ እጽፍልሃለሁ።


የምናዛችሁንም አሁን እንድታደርጉ ወደ ፊትም ደግሞ እንድታደርጉ ስለ እናንተ በጌታ ታምነናል።


ቃሌን ለውጬ አሁን በእ​ና​ንተ ዘንድ ልገኝ እሻ​ለሁ፤ ስለ እና​ንተ የም​ና​ገ​ረ​ውን አጣ​ለ​ሁና።


ስለ እና​ንተ በከ​ንቱ ደክሜ እንደ ሆነ ብዬ እፈ​ራ​ች​ኋ​ለሁ።


ስለ​ዚ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለማ​ፍ​ረስ ያይ​ደለ ለማ​ነጽ በሰ​ጠን ሥል​ጣን ወደ እና​ንተ በመ​ጣሁ ጊዜ ቍርጥ ነገር እን​ዳ​ላ​ደ​ር​ግ​ባ​ችሁ፥ ሥል​ጣን እን​ዳ​ለው ሰው ከእ​ና​ንተ ጋር ሳል​ኖር ይህን እጽ​ፋ​ለሁ።


ወደ እና​ንተ በመ​ጣሁ ጊዜ እሠ​ራ​ለሁ፤ በሥ​ጋዊ ሥር​ዐ​ትም እን​ደ​ም​ን​ኖር አድ​ር​ገው በሚ​ጠ​ረ​ጥ​ሩን ሰዎች ላይ በድ​ፍ​ረት ለመ​ና​ገር አስ​ባ​ለሁ፤ እና​ንተ ግን በዚህ ዓይ​ነት ድፍ​ረት እን​ድ​ና​ገር እን​ዳ​ታ​ደ​ር​ጉኝ እለ​ም​ና​ች​ኋ​ለሁ።


በብዙ የፈ​ተ​ን​ነ​ው​ንና በሁ​ሉም ነገር ትጉህ ሆኖ ያገ​ኘ​ነ​ውን አሁ​ንም በእ​ና​ንተ እጅግ ስለ​ሚ​ታ​መን ከፊት ይልቅ እጅግ ትጉ የሚ​ሆ​ነ​ውን ወን​ድ​ማ​ች​ንን ከእ​ነ​ርሱ ጋር እን​ል​ካ​ለን።


እኔም በሁሉ ነገር እተ​ማ​መ​ና​ች​ኋ​ለ​ሁና ደስ ይለ​ኛል።


ስለ​ዚህ ከአ​ሁን ጀምሮ በሥጋ የም​ና​ው​ቀው የለም፤ ክር​ስ​ቶ​ስ​ንም በሥጋ ብና​ው​ቀው አሁን ግን ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ የም​ና​ው​ቀው አይ​ደ​ለም።


እን​ደ​ዚህ ላለው ሰው ከእ​ና​ንተ ከብ​ዙ​ዎች ያገ​ኘ​ችው ይህች ተግ​ሣጽ ትበ​ቃ​ዋ​ለች።


በዚ​ህም ታምኜ ጸጋን በዕ​ጥፍ እን​ድ​ታ​ገኙ በመ​ጀ​መ​ሪያ ወደ እና​ንተ እመጣ ዘንድ መከ​ርሁ።


ቀድ​ሞስ በመ​ል​ካም ተፋ​ጥ​ና​ችሁ ነበር፤ በእ​ው​ነት እን​ዳ​ታ​ምኑ ማን አሰ​ና​ከ​ላ​ችሁ?


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios